በኬፕ ታውን ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸነፉ

- Advertisement -
Sidebar AD

በሳንላም ኬፕ ታውን የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸንፈዋል፡፡

በወንዶች አትሌት መሀመድ ኢሳ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ55 ሴኮንድ በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቅቋል፡፡

በርቀቱ የተሳተፈው ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ይሁንልኝ አዳነ 2 ሰዓት ከ4 ደቂቃ ከ59 ሴኮንድ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ ውድድሩን ጨርሷል፡፡

በሴቶች ደግሞ አትሌት ደራ ዲዳ 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ18 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት በመግባት 1ኛ በመሆን አጠናቅቃለች፡፡

በርቀቱ የተሳተፉት ሌሎች ኢትየጵያዊያን አትሌቶች መስታወት ፍቅር እና ዋጋነሽ አማረ 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን ይዘው ውድድራቸውን ጨርሰዋል፡፡

ኤፍ ኤም ሲ






Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: