#Ethiopia | ናሚቢያ ሀገሪቱ ከጠቅላላ ግዛቷ ውስጥ ከ40 በመቶ በላይ የሚሆነውን መሬት ለተፈጥሮ ጥበቃ የከለለች ሲሆን፣ የአካባቢ ጥበቃና መብትን በሕገ-መንግሥቷ ውስጥ አካትታ ያጸደቀች የመጀመሪያዋ የአፍሪካ ሀገር ናት።
ሀገሪቱ በዓለም አቀፉ የዘላቂ ቱሪዝም ምክር ቤት መመዘኛዎች መሠረት ወደ 95 በመቶ የሚጠጋ ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበች ሲሆን፣ ማኅበረሰብ-ተኮር የዱር እንስሳት ጥበቃ ማኅበራት የዱር እንስሳቱን የመንከባከብ ኃላፊነት ወስደው እየሠሩ ይገኛሉ።
እነዚህ ማኅበራት ከቱሪዝም የሚገኘውን ገቢ በቀጥታ ለአካባቢው ነዋሪዎች በማከፋፈል ረገድም ትልቅ ሚና እየተጫወቱ ነው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በተፈጥሮና በባህላዊ እሴቶች ላይ የሚያተኩረው ሥነ-ምህዳራዊ ቱሪዝም በሀገሪቱ በከፍተኛ ደረጃ እየተስፋፋ ይገኛል፤ ይህም በአካባቢው ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት የማያደርሱና ለተፈጥሮ ጥበቃ ትኩረት የሚሰጡ በርካታ ጎብኚዎችን ወደ ናሚቢያ እየሳበ መሆኑ ታውቋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Source: GetuTemesgen









No comments yet.