ዋሽንግተን ከአስርት ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢራን ነዳጅ በአሜሪካ ዶላር እንዲሸጥ በመፍቀድ ቴህራን ላይ የጣለችውን ማዕቀብ በጊዜያዊነት አነሳች።
ለ60 ቀናት የሚቆየውን የማዕቀብ ማላላት እርምጃ ሰኞ ምሽት ይፋ ያደረገው የአሜሪካ ግምጃ ቤት ነው። ይህ እርምጃ የኢራንን ኢኮኖሚ አንቆ የያዘው እና ለረጅም ጊዜ የቆየው የአሜሪካ ማዕቀብ ዋነኛ ምሰሶዎች እንዲወገዱ ያደርጋል።
በዚህ የአስቸኳይ ጊዜ ፈቃድ መሠረት ኢራን እስከ ነሐሴ ወር ድረስ ድፍድፍ ነዳጅ እንዲሁም የፔትሮኬሚካል ምርቶችን ማምረት፣ መሸጥ እና መላክ ትችላለች። ይህ የማዕቀብ እፎይታ የኢራን ነዳጅ በቀጥታ ወደ አሜሪካ እንዲገባም ያስችላል።
በተጨማሪም የኢራን የባንክ ዝውውር፣ ኢንሹራስ እና ትራንስፖርት ዘርፍ ላይ የተጣለው ማዕቀብ መነሳቱ ቴህራን ከዚህ ቀደም ድፍድፍ ነዳጇን ለመሸጥ ስትከተል የነበረውን ውስብስብ አሰራር ያስቀራል።
የግምጃ ቤት ኃላፊው ስኮት ቤንሰንት እንደተናገሩት ለ60 ቀናት የሚቆይ የማዕቀብ እፎይታ የተሰጣት ኢራን በምላሹ ወሳኙ የባሕር መተላለፊያ የሆነውን የሆርሙዝ ወሽመጥ ለመክፈት ቃል ገብታለች።
የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኤነርጂ ኤጀንሲ የኒውክሌር ተቆጣጣሪዎችም ወደ አገሪቱ እንዲገቡ ትፈቅዳለች ብለዋል።
ኢራን ግን ይህ ተቆጣጣሪዎች ወደ አገሪቱ እንዲገቡ ልትፈቅድ ነው መባሉን አስተባብላለች።
አሜሪካ የማዕቀብ ማላላት እርምጃውን የወሰደችው ስዊዘርላንድ ውስጥ ሁለቱን አገራት ሲያደራድሩ የነበሩት አሸማጋዮች ጥሩ መሻሻል መታየቱን ከገለጹ በኋላ ነው።
ኳታር እና ፓኪስታን ሰኞ ዕለት ባወጡት መግለጫ አሜሪካ እና ኢራን “በ60 ቀናት ውስጥ የመጨረሻ ስምምነት ላይ ለመድረስ የሚያስችል ፍኖተ ካርታ” ላይ መስማማታቸውን አስታውቀዋል።
የአሜሪካው ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስም የፎቶው ባለመብት የመጀመሪያው ዙር ንግግር “በጣም ጥሩ መሠረት” መጣሉን ተናግረዋል።










No comments yet.