የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 16ኛ መደበኛ ጉባኤ የተጓደሉ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን አመራሮችን ሹመት መርምሮ አጸደቀ።
ምክር ቤቱ አመራሮቹን ለመሾም በመስፈርቱ መሠረት ምልመላ ሲያካሄድ ቆይቶ የአራት አመራሮችን ሹመት መርምሮ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል።
በዚሁ መሠረት ሚዛኔ አባተ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር፣ ወ/ሮ አሸነፈች አበበ የሴቶችና ሕፃናት ጉዳዮች ዘርፍ ኮሚሽነር፣ አቶ መሃመድ አህመድ የአካል ጉዳተኞችና አረጋውያን ጉዳዮች ዘርፍ ኮሚሽነር እንዲሁም አቶ በዳሳ ለሜሳ የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል።
ጋዜጣ-ፕላስ

Source: Yeneta Tube








No comments yet.