የአሜሪካ ድርጊት «የማይሳካ» ነው – ፕረዚደንት ሞሱድ ፐዛሽኪያን
የኢራን ፕረዚደንት አሜሪካ እያካሄደች ያለውን የሆርሙዝ ሰርጥ ክልከላ በፐርሺያ ባሕረሰላጤ አለመረጋጋትን የሚያሰፍን ነው ሲሉ ወቀሱ።
ፕረዚደንት ሞሱድ ፐዛሽኪያን ዛሬ ባሰራጩት መልዕክት የአሜሪካን ድርጊት «የማይሳካ» ብለውታል።
የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ደሴቶች የሚወጡም ሆነ የሚገቡ መርከቦች እንቅስቃሴ እንዲታጎል የሰጡትን መመሪያን ተከትሎ በሁለቱም አገራት ተስፋ ተጥሎበት የነበረው ድርድር ለመክሸፉ እንደአንድ ምክንያት ሊሆን መቻሉን መረጃዎች ያመላክታሉ።
ኢራን ክልከላው እንዲነሳ፣ ጦርነቱ ቆሞ የደሕንነት ዋስትና እንዲሰጣት እንዲሁም የኒኩሌር ማበልጸግ ጉዳይ ወደፊት የሚታይ አጀንዳ እንዲሆን የሚሉ የመደራደሪያ ነጥቦችን በፓኪስታን በኩል ወደ አሜሪካ ልካለች።
ዩናይትድ ስቴትስ መደራደሪያ ነጥቦቹ እያጤንኳቸው ነው ብትልም ባሕር ሐይሏ ግን ከኢራን ወደቦች የሚወጡና የሚገቡትን መከልከሉን እንደቀጠለ ነው።
ይህን ተከትሎ ነው ፕረዚደንቱ በመግለጫቸው ክልከላው ለቀጠናው አደገኛ አለመረጋጋትን ያስከትላል ሲሉ ያስጠነቀቁት።
@seledadotio
@seledadotio
የኢራን ፕረዚደንት አሜሪካ እያካሄደች ያለውን የሆርሙዝ ሰርጥ ክልከላ በፐርሺያ ባሕረሰላጤ አለመረጋጋትን የሚያሰፍን ነው ሲሉ ወቀሱ።
ፕረዚደንት ሞሱድ ፐዛሽኪያን ዛሬ ባሰራጩት መልዕክት የአሜሪካን ድርጊት «የማይሳካ» ብለውታል።
የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ደሴቶች የሚወጡም ሆነ የሚገቡ መርከቦች እንቅስቃሴ እንዲታጎል የሰጡትን መመሪያን ተከትሎ በሁለቱም አገራት ተስፋ ተጥሎበት የነበረው ድርድር ለመክሸፉ እንደአንድ ምክንያት ሊሆን መቻሉን መረጃዎች ያመላክታሉ።
ኢራን ክልከላው እንዲነሳ፣ ጦርነቱ ቆሞ የደሕንነት ዋስትና እንዲሰጣት እንዲሁም የኒኩሌር ማበልጸግ ጉዳይ ወደፊት የሚታይ አጀንዳ እንዲሆን የሚሉ የመደራደሪያ ነጥቦችን በፓኪስታን በኩል ወደ አሜሪካ ልካለች።
ዩናይትድ ስቴትስ መደራደሪያ ነጥቦቹ እያጤንኳቸው ነው ብትልም ባሕር ሐይሏ ግን ከኢራን ወደቦች የሚወጡና የሚገቡትን መከልከሉን እንደቀጠለ ነው።
ይህን ተከትሎ ነው ፕረዚደንቱ በመግለጫቸው ክልከላው ለቀጠናው አደገኛ አለመረጋጋትን ያስከትላል ሲሉ ያስጠነቀቁት።
@seledadotio
@seledadotio









No comments yet.