በሰው ላይ ጥቃት በማድረስ የተከሰሰው ድምፃዊ አህመድ ማንጁስ የ300 ብር ቅጣት እንዲከፍል ተፈረደበት።
በሴት ልጅ ላይ አካላዊ ጥቃት በማድረስ ወንጀል የተከሰሰው ድምፃዊ አህመድ ሁሴን ወይንም ማንጁስ ላይ የገንዘብ ቅጣቱን ያስተላለፈው ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎት ነው።
ድምፃዊው ለዚህ ቅጣት የተዳረገው የካቲት 22 ቀን 2018 ዓመተ ምህረት ከንጋቱ 12 ሰዓት ከ10 ላይ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ስታር ሆቴል በተባለው ውስጥ የግል ተበዳይ የሆነችውን መድሃኒት ይልማ ላይ ጥቃት ፈጽሞ ጥፋተኛ በመባሉ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ውሳኔ ላይ አብራርቷል።
ፍርድ ቤቱ የቅጣት ውሳኔውን ከመስጠቱ በፊት የግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት የመረመረ ሲሆን፣ አቃቤ ህግ ወንጀሉ የተፈጸመው በሴት ላይ በመሆኑና ተከሳሽ ድርጊቱን የፈጸመው በምሽት በመሆኑ ቅጣቱ ሊከብድበት ይገባል ሲል አመልክቷል።
ተከሳሽ በበኩሉ ቀደም ሲል የጥፋተኝነት ሪከርድ የሌለበት መሆኑን፣ ድርጊቱን መፈጸሙን አምኖ በመጸጸቱ እንዲሁም የሁለት ልጆች አባትና የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆኑን በመጥቀስ የሚጣልበት ቅጣት እንዲቀልለት ጠይቋል።
ፍርድ ቤቱ በውሳኔው የአቃቤ ህግን የቅጣት ማክበጃ በመተው፣ ተከሳሹ ያቀረባቸውን የቅጣት ማቅለያዎች ተቀብሎ የእስራት ቅጣቱን ወደ ገንዘብ ቅጣት ቀይሮለታል።
በዚህም መሰረት ተከሳሹ የ300 ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍል እንደተወሰነበት በፍርድ ቤቱ በሰጠው ውሳኔ ላይ ተመልክተናል።
Via ኢትዮጲካሊንክ
@seledadotio
@seledadotio
በሴት ልጅ ላይ አካላዊ ጥቃት በማድረስ ወንጀል የተከሰሰው ድምፃዊ አህመድ ሁሴን ወይንም ማንጁስ ላይ የገንዘብ ቅጣቱን ያስተላለፈው ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቂርቆስ ምድብ ችሎት ነው።
ድምፃዊው ለዚህ ቅጣት የተዳረገው የካቲት 22 ቀን 2018 ዓመተ ምህረት ከንጋቱ 12 ሰዓት ከ10 ላይ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ስታር ሆቴል በተባለው ውስጥ የግል ተበዳይ የሆነችውን መድሃኒት ይልማ ላይ ጥቃት ፈጽሞ ጥፋተኛ በመባሉ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ውሳኔ ላይ አብራርቷል።
ፍርድ ቤቱ የቅጣት ውሳኔውን ከመስጠቱ በፊት የግራ ቀኙን የቅጣት አስተያየት የመረመረ ሲሆን፣ አቃቤ ህግ ወንጀሉ የተፈጸመው በሴት ላይ በመሆኑና ተከሳሽ ድርጊቱን የፈጸመው በምሽት በመሆኑ ቅጣቱ ሊከብድበት ይገባል ሲል አመልክቷል።
ተከሳሽ በበኩሉ ቀደም ሲል የጥፋተኝነት ሪከርድ የሌለበት መሆኑን፣ ድርጊቱን መፈጸሙን አምኖ በመጸጸቱ እንዲሁም የሁለት ልጆች አባትና የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆኑን በመጥቀስ የሚጣልበት ቅጣት እንዲቀልለት ጠይቋል።
ፍርድ ቤቱ በውሳኔው የአቃቤ ህግን የቅጣት ማክበጃ በመተው፣ ተከሳሹ ያቀረባቸውን የቅጣት ማቅለያዎች ተቀብሎ የእስራት ቅጣቱን ወደ ገንዘብ ቅጣት ቀይሮለታል።
በዚህም መሰረት ተከሳሹ የ300 ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍል እንደተወሰነበት በፍርድ ቤቱ በሰጠው ውሳኔ ላይ ተመልክተናል።
Via ኢትዮጲካሊንክ
@seledadotio
@seledadotio
Related Posts
- Advertisement -









No comments yet.