የጋዛ የባህር ዳርቻ የፈተና ማዕከል ሆነ

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | በእስራኤል እና በሃማስ መካከል በቀጠለው ጦርነት ምክንያት የጋዛ የትምህርት ተቋማት ቢፈራርሱም ተማሪዎች ግን በሜዲትራኒያን ባህር ዳርቻ ላይ ሆነው የመጨረሻ ፈተናቸውን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ።

ትምህርት በማንኛውም ሁኔታ በሚል መርህ የተጀመረው ይህ ጥረት እንደ ኢያድ ያሉ የኢንጂነሪንግ ተማሪዎች አሸዋ ላይ ተቀምጠውና ፕላስቲኮችን እንደ ጠረጴዛ ተጠቅመው የወደፊት እጣ ፈንታቸውን እንዲወስኑ አስችሏቸዋል።

ይህ ትዕይንት የመማሪያ ክፍሎች ቢወድሙም የእውቀት ጥማት እንደማይገታ ለዓለም ያሳየ የጽናት ማሳያ ሆኖ ተመዝግቧል።

በጋዛ የትምህርት ዘርፉ ላይ እየደረሰ ያለው ጉዳት እጅግ ከፍተኛ ሲሆን የፍልስጤም ትምህርት ሚኒስቴር ድርጊቱን የትምህርት ጭፍጨፋ ሲል ጠርቶታል።

እስከ ግንቦት 2026 ድረስ ባለው መረጃ ከ20 ሺህ በላይ ተማሪዎች እና 1 ሺህ የሚጠጉ መምህራን ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን በርካታ ታዋቂ ፕሮፌሰሮችም ተገድለዋል።

እስራኤል የትምህርት ተቋማቱ ለወታደራዊ ዓላማ ይውሉ ነበር የሚል ክስ ብታቀርብም የፍልስጤም ባለስልጣናት ግን ጥቃቱ ምሁራንን ለማጥፋት የታለመ የጦር ወንጀል ነው በማለት ዓለም አቀፍ ምርመራ እንዲደረግ እየጠየቁ ይገኛሉ።

የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር አምጃድ ባርሀም እንደገለጹት ተማሪዎቹ በአሸዋ ላይ ሆነው የሚፈተኑት ምስል የማይበገረው የፍልስጤማውያን ፍላጎት ማሳያ ነው።

እ.ኤ.አ በ2026 ይፋ የተደረገው ትምህርት በየትኛውም ቦታ ስትራቴጂ በፈራረሱ ህንጻዎች ፋንታ ክፍት ቦታዎችን ለትምህርት መጠቀምን ያለመ ነው።

ሚኒስትሩ ይህ በእውቀት የሚደረግ ትግል መሆኑን ገልጸው እያንዳንዱ ተማሪ ትምህርትን እንደ ነፃነት መሳሪያ እየተጠቀመበት እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

#palestine #gaza #education #war #resilience #humanrights #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: