በአለም ዋንጫ ታሪክ የመጀመሪያው ሶማሊያዊ ዳኛ ለመሆን የታጨው ዑመር አርታን ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ተከለከለ በአለም አቀፉ የ…

- Advertisement -
Sidebar AD
በአለም ዋንጫ ታሪክ የመጀመሪያው ሶማሊያዊ ዳኛ ለመሆን የታጨው ዑመር አርታን ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ተከለከለ
በአለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) እውቅና ያገኘውና በ2026ቱ የአለም ዋንጫ ላይ እንዲዳኝ ተመርጦ የነበረው ዑመር አርታን፣ ወደ አሜሪካ ለመግባት ያደረገው የቪዛ ጥያቄ ውድቅ ተደርጎበታል።
ይህ ውሳኔ በሶማሊያ ስፖርት አፍቃሪያን ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታን ፈጥሯል።
​የቪዛው መከልከል ግልፅ ምክንያት ባይቀመጥም፣ ውሳኔው ዳኛው በታሪካዊው መድረክ ላይ የመሳተፍ ህልሙን አደጋ ላይ ጥሎታል።
ፊፋ እና የሶማሊያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጉዳዩን ለማስቀየር ዲፕሎማሲያዊ ጥረት እያደረጉ ቢሆንም፣ ጥብቅ የሆነው የአሜሪካ የቪዛ ፖሊሲ ትልቅ ማነቆ ሆኗል።
በአፍሪካ ዋንጫ ላይ ድንቅ ብቃቱን ያሳየው አርታን፣ ይህ እገዳ ካልተነሳለት ታላቁን የስፖርት መድረክ ያጣዋል።
ቢቢሲ ስፖርት
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2