#FastMereja I በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባምባሲ ወረዳ በማህበራዊ ሚዲያ (በተለይም በቲክቶክ) ላይ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችን የሚያንቋሽሹ፣ የሚሳደቡ እና የማህበረሰቡን ወግና ልማድ የሚፃረሩ ጸያፍ ቃላትን ሲነዙ የነበሩ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት አዛዥ ኮማንደር ሀሩን ሄረላ እንደገለጹት፣ ተጠርጣሪዎቹ የዲጂታል መድረኮችን በመጠቀም የህዝብን ሞራልና የአካባቢውን ሰላም የሚነኩ ተግባራትን ሲፈጽሙ ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት በግለሰቦቹ ላይ ጥብቅ የምርመራ ሂደት እየተከናወነ ሲሆን፣ የምርመራው ውጤት ተጠናቆ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለህብረተሰቡ ይፋ እንደሚደረግ ፖሊስ ተናግሯል።
Source: FastMereja








No comments yet.