እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ነገር ትከልለን፤ ምልጃዋ እና ረድኤቷም አይለየን

- Advertisement -
Sidebar AD

🙏

ልጇን ይዛ ወደ ግብፅ ተሰደደች

የአዳም ተስፋው እውን ሊሆን አምስት ሺ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም በሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል ብስራት በድንግል ማሕጸን አደረ፡፡ የማይቻለውን ቻለችው፣ የማይወሰነውንም ወሰነችው፡፡ ሰማይና ምድርን የፈረጠረውን ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በሰማይ ዙፋኑ ሳይጎድል ማኅጸኗን ዓለም አድርጎ ተቀመጠ፡፡ በመጨረሻም በታሕሳስ 29 ቀን በበረት ተወለደ፤ በጨርቅ ተጠቀለለ፣ ሰውና መላዕክት በአንድ ላይ አመሰገኑት፤ ሰብዓ ሰገልም ገበሩለት፡፡ ጌታችን 2 ዓመት ሲሞላው ንጉስ ሔሮድስ ንጉስ መወለዱን ከሰብዓ ሰገል ሲሰማ ሊገድለው ተነሳ። የእግዚአብሔር መልአክም ለዮሴፍ በሕልም ተገልጾ “ተነስተህ እናቱንና ብላቴናውን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ” ብሎ ነገረው፡፡ ይህ የእመቤታችን ስደትም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ለማሰብም ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 6 ወርኀ ጽጌ፣ ዘመነ ጽጌ የአበባ ዘመን እየተባለ ይታሰባል፡፡

እመቤታችንም ከዮሴፍ ጋር ልጇን ይዛ ወደ ግብፅ ተሰደደች፡፡ እድስት ድንግል ማርያም ከተወደደ ልጇ ጋር ወደ ግብፅ በተሰደደችበት ጊዜ ብዙ መከራ ገጥሟታል፡፡ ልጇን ከሞት ለማዳን ብዙ ችግር አይታለች፡፡ የቀን ሐሩር፣ የሌሊት ቊር እየተፈራረቀባት፣ እሾሁ እየወጋት፣ እንቅፋቱ እየመታት፣ መውጫና መግቢያው በማይታወቅ በረሃ ውስጥ ብዙ ተሰቃይታለች፡፡ ሕፃኑን ልጇን ለመግደል ባለ ኃይሉ ይጥር የነበረው ሄሮድስ አራት ወታደሮቹን ከእነጭፍሮቻቸው ሸልሞ እመቤታችንን ከነልጇ ይዘው ከመጡ የበለጠ ሹመትና ሽልማት እንደሚሰጣቸው ነግሮ ላካቸው፡፡ የዮሴፍ ልጅ ዮሳ ይህንን ሰምቶ ሲነግራቸው ቅድስት ድንግል ማያርም ምርር ብላ አልቅሳለች፡፡ የቅዳሴ ማርያም አንድምታ ወይም ትርጓሜ እንደሚነግረን በግብፅ በርሃ ሲጓዙም እመቤታችን ወደ ትዕማን ቤት ሄደች፡፡ ይሁንና ያቺ ሴትና አገልጋዩዋ በእመቤታችንና በዮሴፍ ላይ ተዘባበቱ፡፡

በእናቱ እቀፍ የነበረውን ጌታችንንም አገልጋይዋ ኮቲባ ከእናቱ እቅፍ ነጥቃ መሬት ላይ ጣለችው፡፡ ጌታም ትዕማንንና ኮቲባን አጥፍቷቸው በቤቱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇና ከዮሴፍ እንዲሁም አብራት ወደ ስደት ከመጣችው ሰሎሜ ጋር ለስድስት ወር ያህል ከተቀመጡ በኋላ ጉዟቸውን ዱር ለዱር አደረጉ፡፡ ይህም እመቤታችን ልጇን እንዳይገሉባት ነበር፡፡
ነገር ግን በስቅለት ዕለት በግራውና በቀኙ የተሰቀሉት ወንበዴዎች ጥጦስና ዳክርስ አገኟቸው፡፡ የጌታን ልብስ ገፈውም ቁመው ሲማከሩ እመቤታችን ልጇን የሚገድሉባት መስሏት አለቀሰች፡፡ ሆኖም ግን ጥጦስ ካደረበት ፍቅርና ርኅራኄ የተነሳ “እነዚህ ሰዎች አሳዘኑኝ! ወደዚህ ቦታ የመጡት ያለ ምክንያት አይሆንምና አንቀማቸው እንተውላቸው” ብሎ ልብሳቸውን መልሶላቸው ጉዟቸውን እንዲቀጥሉ ረዳቸው፡፡ በምድረ ግብጽ በስደት 42 ወራት አሳልፋለች፡፡

በየዓመቱ ኅዳር 6 እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከተወደደ ልጇ፣ ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር በሄሮድስ ምክንያት የደረሰባቸው ስደትና መከራ አልፎ ደብረ ቁስቋም በተባለች ቦታ ያረፉበት ነው፡፡ በማቴዎስ 2÷20 እንደተጻፈው “ሄሮድስም በሞተ ጊዜ እነሆ የእግዚአብሔር መልአክ በግብፅ ሀገር ለዮሴፍ በሕልም ታየው፡፡ የሕፃኑን ነፍስ የሚሹ ሙተዋልና ተነሥተህ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ እስራኤል ሀገር ሂድ አለው፡፡” አረጋዊው ዮሴፍም ሰሎሜ እያገዘችው የሚያገለግላትን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከተወደደ ልጇ ጋር ይዞ ከስደት ተመልሰዋል፡፡ ገዳማውያን ይሕን የስደቷን ጊዜ በጾምና ጸሎት ያስቡታል፤ በረከትም ያገኙበታል፡፡ ከበረከታቸው እንሳተፍ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡

ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም

ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444

ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957


Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1