ጥርስን በቀን ሁለት ጊዜ ጠዋትና ማታ ማፅዳት ይመከራል።
ይሁን እንጅ በበርሚንግሃም ዩኒቨርሲቲ የጥርስ ትምህርት ክፍል ጥርስዎን ሲያፀዱ ይህን ቢያደርጉ ሲል ይመክራል።
በቀን አንድ ጊዜ ማፅዳት፦ ከድግግሞሽ ይልቅ በደንብ አንድ ጊዜጥርስዎን ቢቦርሹት የተሻለ ነው።
ይህንንም በጥርሶች መሃል በተዘጋጀ ቀጭንና ጠንካራ ክር በማስገባት ማፅዳት (ፍሎስ) በማድረግ መታገዝ አለበት።
ከቁርስ በፊት ማድረግ፦ ከተመገቡ በኋላ ጥርስዎን ከቦረሹ ከምግብ የሚመነጩ አሲዶች የጥርስ ግድግዳን የማሳሳት አቅም ያገኛሉ።
ስለዚህ ከመመገብዎ በፊት ጥርስዎን ቢቦርሹ፤ ካልሆነ ግን ከተመገቡበኋላ አፍን በውሃ መጉመጥመጥና ቢያንስ ከ30 ደቂቃ በኋላ ቢቦርሹ።
አለመጉመጥመጥ፦ ጥርስን ቦርሾ መጉመጥመጥ ጥርስን የሚከላከለውን ግድግዳ ያሳሳዋል።
ስለዚህ ቦርሸው ያለውሃ መትፋት እንጅ በውሃ መጉመጥመጥ የጥርስጥንካሬን እና መስታዎቱን