የደቡብ ሱዳን ተቃዋሚ ጄኔራል መታሰር የሰላም ስምምነቱን የሚጥስ እንደሆነ ተገለጸ

- Advertisement -
Sidebar AD

የደቡብ ሱዳን ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲ ወታደራዊ ክንፍ የጦር አዛዥ ጄነራል መታሰር ለአምስት ዓመታት የዘለቀውን የእርስ በርስ ጦርነት የቋጨውን የሰላም ስምምነት “የጣሰ ነው” ሲሉ የተቃዋሚው ቃለ አቀባይ ተናገሩ።
ጄኔራል ጋብርኤል ዲዮፕ ላም እንዲሁም በተቃውሞ ላይ ያለው የሱዳን ህዝቦች ነጻ አውጪ ንቅናቄ (ኤስፒኤልኤም-አይኦ) ከፍተኛ ባለስልጣናት በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ለእስር ተዳርገዋል።
በቁጥጥር ስር የዋሉት የጦር ጄነራል እና ከፍተኛ ባለስልጣናቱ በአውሮፓውያኑ 2013 ከፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ጋር ከፍተኛ ሽኩቻ ውስጥ የገቡት የምክትል ፕሬዚዳንቱ ሪክ ማቻር አጋር ናቸው። በሳልቫ ኪር እና በምክትላቸው የተነሳው የስልጣን ውጥረት አገሪቷን ደም አፋሳሽ ወደሆነ የርስ በርስ ጦርነት ውስጥ መክተቱ ይታወሳል።
ሐሙስ ጥዋት የማቻር ቃል አቀባይ ፓርቲያቸው ባለስልጣኖቻቸው የት እንዳሉ ወይም የት እንደታሰሩ አያውቅም ብለዋል።
“ሁኔታዎች የበለጠ እንዳይባባሱ የተቻለንን ሁሉ እናደርጋለን፤ ነገር ግን ይህች አገር ዳግም ወደ ጦርነት እንዳትመለስ የፖለቲካ ቁርጠኝነቱን ማሳየት ያላባቸው የሰላም አጋሮቻችን ናቸው ሲሉ ፑዎክ ቦዝ ባሉዋንግ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ደቡብ ሱዳን ተመልሳ ወደ ጦርነት አትገባም ሲሉ መናገራቸውን የመንግሥት ቃል አቀባይ ማኩዩ ረቡዕ ዕለት በመዲናዋ ጁባ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። የተቃዋሚዎቹ ባለስልጣናት የታሰሩት “ከህግ ጋር በመጋጨታቸው” እንደሆነ ቃል አቀባዩ አክለዋል።

Via BBC



Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: