#Ethiopia | የናሚቢያ ሪፐብሊክ ቀዳማዊት እመቤት ሱስትጂ ምቡምባ ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ሙሉ ለሙሉ በሴቶች የተመራውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በሆሴአ ኩታኮ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በመቀበል አክብረዋል።
ቀዳማዊት እመቤቷ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሙሉ ሴት ሠራተኞች የያዘውን በረራ በተቀበሉበት ወቅት “ሴቶች ወደ ላይ ሲወጡ ዓለም ከእነርሱ ጋር ይነሳል” ብለዋል።
በረራውን የእድገት ምልክት ብለው የጠሩትም ሲሆን፣ ለጾታ እኩልነት የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት መናገራቸውን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሐን ዘግቧል።

Source: GetuTemesgen









No comments yet.