ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የዓድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ምስረታን አበሠሩ

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | የዓድዋ ድል ማይክሮ ፋይናንስ አክሲዮን ማህበር የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በተገኙበት በይፋ ተመስርቷል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በዚህ ወቅት÷ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ አክሲዮን ማህበር እንዲቋቋም ጥረት ሲደረግ እንደነበር አስታውሰው አሁን ላይ በቀጥታ ወደ ሥራ በመግባት አክሲዮን ማህበሩ መመስረቱን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው ወታደራዊ አክሲዮን ማህበር የተቋሙን የፋይናንስ ዘርፍ ለማሣደግ የሚያግዝ ከመሆኑም በላይ የሠራዊቱን ፋይናንሻል ተጠቃሚነት እንደሚያጠናክር አንስተዋል፡፡

ቅርንጫፎችን በማብዛት በሁሉም ቦታ ተደራሽና ፈጣን አገልግሎት ሠጪ ለመሆን መሥራት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

የመከላከያ ፋውንዴሽን ሪፎርሙን ተከትሎ እንደ አዲስ ከተደራጀ ወዲህ በበርካታ ዘርፎች ለሠራዊቱ የማህበራዊ ዋስትና ሆኖ እየሠራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ከፍተኛ የአክሲዮን ግዥ የፈፀሙ ዕዞች፣ ኮሮችና ዋና መምሪያዎች የተዘጋጀላቸውን የዋንጫ ሽልማትና ሠርተ-ፊኬት ከፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ መቀበላቸውንም የመከላከያ ሰራዊት መረጃ ያመላክታል።
#fmc
ባሉበት ሆነው ትኩስ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኝት ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

“””””””””””***””””””””””
ዩቲዩብ ገጽ: https://www.youtube.com/@getutemesgenet

ፌስቡክ ገጽ: https://web.facebook.com/getu26

ቴሌግራም ገጽ: https://t.me/getutemesgenet

ቲክቶክ ገጽ: https://www.tiktok.com/@getutemesgenet

ኢንስታግራም ገጽ: https://www.instagram.com/getutemesgenet

ኤክስ: https://x.com/getutemesgenet

አማርኛ ድረ-ገጽ: https://getutemesgen.et

ኢንግሊዘኛ ድረ-ገጽ: https://en.getutemesgen.et





Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1