#Ethiopia | የኢትየጵያ ፕሬስ ድርጅት ያዘጋጀው ሁለተኛ ምዕራፍ ሶስተኛ ዙር “ስለኢትዮጵያ” የፎቶግራፍ ዓውደ-ርዕይ እና የፓናል ውይይት በአዲስ አበባ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት እየተካሄደ ነው።
የሁለተኛው ምዕራፍ ሶስተኛው ዙር “ስለኢትዮጵያ” መርሀ-ግብር “ክህሎት ስለኢትዮጵያ” በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ ይገኛል።
በመክፈቻው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚልን ጨምሮ፣ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡሉልታ፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር)፣ አቶ ዳንኤል ተሬሳ፣ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፀዳለ ተክሉ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ሁለተኛው ምዕራፍ የመጀመሪያው ዙር “ስለኢትዮጵያ” መድረክ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቡታጅራ ከተማ ሁለተኛው ዙር ደግሞ በሐረር ከተማ መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 17 መድረኮች ተዘጋጅተው ስለኢትዮጵያ እንደተመከረበት ተመላክቷል።
Photo Credit: amn
ባሉበት ሆነው ትኩስ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኝት ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።
“””””””””””***””””””””””
ዩቲዩብ ገጽ: https://www.youtube.com/@getutemesgenet
ፌስቡክ ገጽ: https://web.facebook.com/getu26
ቴሌግራም ገጽ: https://t.me/getutemesgenet
ቲክቶክ ገጽ: https://www.tiktok.com/@getutemesgenet
ኢንስታግራም ገጽ: https://www.instagram.com/getutemesgenet
ኤክስ: https://x.com/getutemesgenet
አማርኛ ድረ-ገጽ: https://getutemesgen.et
ኢንግሊዘኛ ድረ-ገጽ: https://en.getutemesgen.et



Source: GetuTemesgen









No comments yet.