ሀሰተኛ ዶላር ለቪዛ አገልግሎት ክፍያ በመፈጸም የተጠረጠረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ

- Advertisement -
Sidebar AD

ሀሰተኛ የአሜሪካ ዶላር ከትክክለኛው ጋር በመቀላቀል ለቪዛ አገልግሎት ክፍያ በመፈጸም የተጠረጠረን ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያደረገ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

ተጠርጣሪው ድርጊቱን የፈጸመው የካቲት 29 ቀን 2017 ዓ.ም በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ጎተራ አካባቢ ከሚገኘው የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት መስሪያ ቤት ውስጥ መሆኑ ተገልጿል።

ተጠርጣሪው 3 ሺህ 500 ሀሰተኛ ዶላር ከትክክለኛ 3 ሺህ 250 የአሜሪካ ዶላር ጋር በመቀላቀል ለቪዛ አገልግሎት ክፍያ ለመፈጸም ሲሞክር በመስሪያ ቤቱ ሰራተኞች እጅ ከፍንጅ መያዙ ተመላክቷል።

ፖሊስ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ካዋለ በኋላ የሰው እና የሰነድ ማስረጃዎችን በማሰባሰብ ተገቢውን የምርመራ ስራ እያከናወነ መሆኑንም ገልጿል።

የውጭ ሀገራትንም ሆነ የኢትዮጵያን ብር እያባዙ ሀሠተኛ ገንዘቦችን ወደ ተቋማት እና ህብረተሰቡ ማሰራጨት እና መገልገል የከፋ ጉዳት እንደሚያስከትል የገለጸው ፖሊስ፣ በእንደዚህ ዓይነት ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ማሳሰቡን ከአዲስ አበባ ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Via AMC



Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: