ጥንቃቄ የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን “ታኪሎ ኢንቨስትመንት ባንክ” ሕገ-ወጥ ነዉ ሲል አስጠነቀቀየኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ…

- Advertisement -
Sidebar AD
❗️ጥንቃቄ ❗️የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን “ታኪሎ ኢንቨስትመንት ባንክ” ሕገ-ወጥ ነዉ ሲል አስጠነቀቀ
የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን “ታኪሎ ኢንቨስትመንት ባንክ” በሚል ስም የሚንቀሳቀስ አካል ያለ ምንም ህጋዊ ፈቃድ የኢንቨስትመንት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አሳውቋል።
ባለስልጣኑ ይህ አካል የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ባንክ ነኝ ብሎ ድረ-ገጽ ከፍቶ ማስተዋወቁን ገልጿል።
ባለስልጣኑ ባወጣው መግለጫ መሰረት ታኪሎ ኢንቨስትመንት ባንክ በካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 980/2016 መሰረት ፈቃድ ሳያገኝ አገልግሎት እየሰጠ ነው። በዚህም ምክንያት በኢትዮጵያ ውስጥ የካፒታል ገበያ አገልግሎት እንዲሰጥ ያልተፈቀደለት አካል መሆኑን አሳስቧል።
በተጨማሪም ባለስልጣኑ የካፒታል ገበያ አገልግሎት መስጠት የሚችሉት በህጋዊ መንገድ የተመዘገቡና ፈቃድ ያላቸው አካላት ብቻ መሆናቸውን አስገንዝቧል።
ግለሰቦች እና ድርጅቶች ከዚህ አካል ወይም ከሌሎች ፈቃድ ከሌላቸው “የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች” ጋር ማንኛውም አይነት የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ አሳስቧል።
@seledadotio
@seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2