በደብረፂዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ክንፍን የሚደግፉ የትግራይ ኃይል አባላት መቀለ ኤፍኤም 104́.4 እና የከተማዋን ከንቲባ ጽህፈት ቤት ሐሙስ፣ መጋቢት 3/2017 ዓ.ም. ተቆጣጥረዋል።
በተመሳሳይም ይኸው የህወሓት ክንፍ ከዚህ ቀደም በከተማው ምክር ቤት ተመርጠዋል ያላቸውን ረዳኢ በርሔን (ዶ/ር ) ድጋሚ የከተማዋ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል።
በደብረፂዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው የህወሓት ክንፍን የሚደግፉ የትግራይ ኃይል አባላት መቀለ ኤፍኤም 104́.4 እና የከተማዋን ከንቲባ ጽህፈት ቤት ሐሙስ፣ መጋቢት 3/2017 ዓ.ም. ተቆጣጥረዋል።
በተመሳሳይም ይኸው የህወሓት ክንፍ ከዚህ ቀደም በከተማው ምክር ቤት ተመርጠዋል ያላቸውን ረዳኢ በርሔን (ዶ/ር ) ድጋሚ የከተማዋ ከንቲባ አድርጎ ሾሟል።
በፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ የሚመራው የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ከዚህ ቀደም በሌላኛው የህወሓት ክንፍ የተሾሙትን ከንቲባ እንቅስቃሴ በማገድ አቶ ብርሐነ ገብረየሱስን የመቀለ ከንቲባ አድርጎ መሾሙ ይታወሳል።
በሁለቱ የህወሓት ክንፎች መካከል የተፈጠረውን ውጥረት ተከትሎ አንድ ሚሊዮን የሚጠጋ ነዋሪዎች ያሏት መቀለ ያለ ከንቲባ እና ያለ ሕዝባዊ አገልግሎት ለአራት ወራት ቆይታለች።
በደብረ ፂዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የህወሓት ክንፍን የሚደግፉ የትግራይ ሠራዊት አዛዦች መሪነት በተለያዩ የትግራይ ክልል ከተሞች እና ወረዳዎች የሚገኙ የጊዜያዊ አስተዳደር መዋቅሮችን በማፍረስ ጽህፈት ቤቶችን ተቆጣጥረዋል።
እንዲሁም በጊዜያዊ አስተዳደሩ ተሹመው የነበሩ አመራሮችን በመተካት ላይ ይገኛሉ።እየተሾሙ ያሉት አመራሮች በትግራይ ጦርነት ከመቀስቀሱ በፊት ምርጫ ተካሂዶ የተቋቋመው ምክር ቤት የሾማቸው አመራሮች ናቸው።
ለሁለት ዓመት የዘለቀውን የትግራይን ጦርነት የቋጨው የሰላም ስምምነት ተከትሎ የፌደራል መንግሥቱ ተቀባይነት የለውም ባለው ምርጫ የተቋቋመው የትግራይ መንግሥት እንዲፈርስ ተደርጓል።
ሆኖም ጊዜያዊ አስተዳደሩን ለማቋቋም በፈጀው ስድስት ወራት ውስጥ ሕገወጥ በተባለው ምርጫ የተሾሙ አመራሮች የክልሉ ከተሞች እና ዞኖችን ሲያስተዳድሩ ቆይተዋል።
የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተከትሎ የጊዜያዊ አስተዳዳደሩን መሪነት የተረከቡት አቶ ጌታቸው ረዳ አብዛኞቹን አመራሮች በማንሳት በራሳቸው ሾመዋል።
ከዚህ ቀደም የነበሩ የከተማ እና የዞን አመራሮች ከመንግሥት ሥራ በበለጠ የፓርቲውን ተግባራት አስቀድመዋል በማለት በአዳዲስ አመራሮች መተካታቸውም ይታወሳል።
“እኔ በምክር ቤቱ የተሾምኩ ሕጋዊ ከንቲባ ነኝ። በመቀለ ከተማ እና በሌሎች ከተሞች ማቋቋሚያ አዋጅ 341 ማንኛውም ከንቲባን የሚሾመው አሸናፊው ፓርቲ ነው” ሲሉ አዲሱ የመቀለ ከንቲባ ረዳኢ በርሔ መናገራቸውን የክልሉ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
“ሉዓላዊ ሥልጣን የሕዝብ መሆኑ እየታወቀ ይሄንን በመጣስ የከንቲባውን ጽህፈት ቤት በመዝጋት ሕዝብ አገልግሎት እንዳያገኝ ተደርጓል” ያሉት ከንቲባው “አሁን ግን በምክር ቤቱ የተመረጠው ከንቲባ ሥራውን በይፋ ጀምሯል” ሲሉ አስታውቀዋል።
ካለፈው ዓመት አጋማሽ ወዲህ በህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት መካከል በተፈጠረው አለመግባባት፤ ፓርቲው በሊቀመንበሩ ዶ/ር ደብረፂዮን ገብረ ሚካኤል እና በምክትል ሊቀመንበሩ ጌታቸው ረዳ በሚመሩ ቡድኖች ተከፍሎ እየተወዛገበ ይገኛል።
ለወራት በገለልተኝነት ከቆዩት የትግራይ ሠራዊት አዛዦች መካከል አብዛኞቹ በደብረፂዮን ለሚመራው ወገን ድጋፍ መስጠታቸውን ተከትሎ በክልሉ ውስጥ ስጋት ተፈጥሯል።


Source: Yeneta Tube









No comments yet.