ኢትዮጵያ ዳግም ተወከለች

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | Miss Super Model World Wide 2025 በVIP አሸኛኘት ተደረገላት

በሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ ያሸናፊዎች አሸናፊ ዲሲምበር 1 2025 እ.ኢ.አ በቦናንዛ ሆቴል በተደረገው የቁንጅና ውድድር ላይ አንደኛ የወጣችው ሀሴት ደረጀ ስትሆን በዚህ ውድድር ላይ ሁለተኛ የወጣችው ሩታ ይርጋለም ዘንድሮ በፊሊፒንስ ማኔላ ከተማ (Miss Super Model World Wide) 2025 Pageant ኢትዮጵያን በመወከል የምትሳተፍ ይሆናል፡፡

ዘንድሮ በፊሊፕንስ ማኒላ ከተማ የሚዘጋጀው አለም አቀፍ የቁንጅና ውድድር በርካታ ሀገሮች የሚሳተፉበት ትልቅ የቁንጅና ውድድር ሲሆን ይህ ውድድር የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ ለማስተዋወቅ መንግስት እየሰራ የሚገኛውን ስራ ከማስተዋወቅም አንፃር የኢትጵያን መልካም ገፅታ ለውጩ አለም ለማስተዋወቅ የሚረዳ ትልቅ አለም አቀፍ የቁንጅና ውድድር ነው ፡፡

ዛሬ በእለተ 09/10/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 4፡00 ሰዓት ላይ በቤተሰቦቿና በስራ ባልደረቦቿ በተገኙበት በቪአይፒ በኩል ያሸኛኝት ስነ- ስርአት ተከናውኗል ይህን ውድድር ለመሳተፍ አዘጋጆቹና አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህልና ኪነ-ጥበብ ቱሪዝም ቢሮ ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ የኣንበሳውን ድርሻ ተወቷል፡፡

መልካም እድል ለኢትዮጵያ !!!






Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: