#Ethiopia | ለዘመናት የኢትዮጲያን ስም በከፍታ ማስጠራት ያልቻለው የኢትዮጲያ ብሄራዊ ቡድን ቢበዛ ከ10 አመታት በኋላ ኢትዮጲያን የሚያኮራበት ጊዜ ይመጣል ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ይህንን የተናገሩት የመደመር መንግስት በተሰኘ መፅሀፍ ምረቃ ስነስርዓት ላይ ነው፡፡
ስፖርቱን ለማሳደግ ባለፉት ዓመታት ከ 100 በላይ ጥቃቅን ሜዳዎችን ገንብተናል ያሉ ሲሆን፤ ይህ ጅማሮ ነገ ላይ አኩሪ የብሄራዊ ቡድንን ለመገንባት የሚረዳ የልምምድ ሂደት ነው ሲሉ ገልፀውታል፡፡
በኢትዮጲያ አንችልም የሚል ትውልድ ተፈጥሯል ያሉም ሲሆን፤ ነገር ግን ኢትዮጲያ በማንኛውም ሁኔታ ትችላለች ችላም አሳይታለች ሲሉ ተናግረዋል፡፡
የውልሰው
Source: GetuTemesgen









No comments yet.