ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሀዲያና ስልጤ ዞኖች የተገነቡ ሞዴል የገጠር መንደሮችን አስረከቡ

- Advertisement -
Sidebar AD

🇪🇹

#Ethiopia | “ረቡዕ ዕለት በሀላባና በከምባታ ዞኖች የነበረው ሞዴል የገጠር መንደሮች ርክክብ ሥነ-ሥርዓት ቀጥሎ፣ በዛሬው ዕለት በሀዲያና ስልጤ ዞኖች የተገነቡ ቤቶችን አስረክበናል፡፡” ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ሚዲያቸው ላይ ጽፈዋል፡፡

የተገነቡት መንደሮች፦

◻️ ባለሦስት መኝታ መኖሪያ ቤቶች፣

◻️ የማብሰል ባዮጋዝ፣

◻️ የፀኃይ ኃይል ማመንጫ፣

◻️ የዶሮና የንብ ማርቢያ እና

◻️ የእንስሳት በረት የተሟላላቸው ናቸው፡፡

“መርሐ – ግብሩ በተመጣጣኝና አነስተኛ ወጪ ከአካባቢ በሚገኙ ግብዓቶች የተሻለ መኖሪያ ከማስገኘት አንፃር ለገጠሩ ማኅበረሰብ ብልጽግና ያለንን ሕልም የሚያሳይ ነው” ሲሉ ገልጸዋል።

🏡 በአራቱ ዞኖች የተሠራው ሥራ በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች መደገም እንዳለበት አሳስበዋል ያለው ስፑትኒክ ነው።


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1