ታዋቂው የቪዲዮ ማጋሪያ መተግበሪያ ቲክቶክ፣ በአሜሪካ ከተደቀነበት የእገዳ አደጋ ለመዳን ሲባል የአሜሪካውን የቢዝነስ ዘርፉን ለ…

- Advertisement -
Sidebar AD
ታዋቂው የቪዲዮ ማጋሪያ መተግበሪያ ቲክቶክ፣ በአሜሪካ ከተደቀነበት የእገዳ አደጋ ለመዳን ሲባል የአሜሪካውን የቢዝነስ ዘርፉን ለሶስት ግዙፍ የአሜሪካ ኢንቨስተሮች ለመሸጥ ከስምምነት ላይ ደረሰ።
ገዢዎቹ ኦራክል፣ ሲልቨር ሌክ እና ኤምጂኤክስ የተባሉ ኩባንያዎች ናቸው። ይህ ስምምነት ተወዳጁ መተግበሪያ በአሜሪካ ምድር ያለ ምንም ገደብ አገልግሎቱን እንዲቀጥል የሚያስችለው እንደሆነ ተገልጿል።
አሶሼትድ ፕሬስ እንደዘገበው፣ ሽያጩ በመጪው ጃንዋሪ 22 ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል። በስምምነቱ መሠረት የሚቋቋመው አዲሱ የ”ቲክቶክ ዩ.ኤስ.” የሽርክና ኩባንያ የባለቤትነት ድርሻ እንደሚከተለው ተዋቅሯል። አዲሱ የባለሀብቶች ስብስብ በአጠቃላይ 50 በመቶውን ድርሻ ይይዛሉ። ከዚህ ውስጥ ኦራክል፣ ሲልቨር ሌክ እና ኤምጂኤክስ እያንዳንዳቸው 15 በመቶ ድርሻ ይኖራቸዋል። የቲክቶክ እናት ኩባንያ የሆነው የባይትዳንስ ነባር ባለሀብቶች ተባባሪዎች 30.1 በመቶ ይይዛሉ። የቻይናው ኩባንያ ባይትዳንስ በበኩሉ 19.9 በመቶ ድርሻ ብቻ ይዞ ይቆያል።
ይህ ስምምነት የተደረገው የአሜሪካ መንግስት “ቲክቶክ ከቻይናው ኩባንያ ቁጥጥር ካልወጣ በብሔራዊ ደህንነት ስጋት ምክንያት ይታገዳለ” የሚል ህግ ካወጣ በኋላ ነው። የቀድሞው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን የፈረሙት ይህ ህግ [PAFACA Act]፣ መተግበሪያው የአሜሪካውያንን መረጃ ለቻይና መንግስት አሳልፎ ሊሰጥ ይችላል በሚል ስጋት ላይ የተመሰረተ ነበር።
በመጀመሪያው የሥልጣን ዘመናቸው ቲክቶክን ለማገድ ሞክረው የነበሩት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በ2024 ምርጫ አሸናፊ ሆነው ከተመለሱ በኋላ አቋማቸውን በማለዘብ ለእገዳው የተቀመጠውን የጊዜ ገደብ አራዝመውት ነበር።
@seledadotio
@seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1