በኦማን የባህር ዳርቻ አቅራቢያ የሚገኝ የጭነት መርከብ ተመታ​የዩናይትድ ኪንግደም የባህር ንግድ እንቅስቃሴ ድርጅት  እንደዘገበ…

- Advertisement -
Sidebar AD
በኦማን የባህር ዳርቻ አቅራቢያ የሚገኝ የጭነት መርከብ ተመታ
​የዩናይትድ ኪንግደም የባህር ንግድ እንቅስቃሴ ድርጅት  እንደዘገበው፣ ከኦማን በስተሰሜን ምስራቅ 25 የባህር ማይል ርቀት ላይ የሚገኝ አንድ የጭነት መርከብ  ባልታወቀ ጥይት መመታቱ ተረጋግጧል።

ጥቃቱ የተወሰኑ ኮንቴይነሮች ላይ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፣ እስካሁን ድረስ በእሳት መያያዝ ወይም በአካባቢው ላይ የደረሰ የአካባቢ ብክለት እንደሌለ ተገልጿል። ይህ ክስተት ኢራን “የሆርሙዝን ወንዝ ዘግቻለሁ” ማለቷን እና በኢራን የባህር ኃይል እና በአሜሪካ የባህር ኃይል መካከል ያለው ውጥረት ከፍተኛ ደረጃ ላይ በደረሰበት ወቅት የተፈጠረ ነው።
​ በዛሬው ዕለት ብቻ በሆርሙዝ አካባቢ ተመሳሳይ የደህንነት ስጋቶች መታየታቸውን ተከትሎ፣ በአካባቢው ያሉ መርከቦች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎችን እንዲያሳውቁ ጥሪ ቀርቧል።
@seledadotio
@seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: