#Ethiopia | የኢትዮጵያ ኢንሹራንስ ማህበር ፕሬዚዳንት ያሬድ ሞላ(ዶ/ር) “ዲጂታላይዜሽን እና የደንበኞች ታማኝነት በኢትዮጵያ የኢንሹራንስ ኢንዱስትሪ” በሚል ርዕስ ያጠኑትን የምርምር ውጤት ይፋ አድርገዋል። ጥናቱ በዘርፉ ላይ እያንዣበቡ ያሉ ስጋቶችንና መወሰድ ያለባቸውን መፍትሄዎች አመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት የዓለም የኢንሹራንስ አገልግሎት በትልልቅ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችአማካኝነት ከፍተኛ ለውጥ እየታየበት ይገኛል። ጥናቱ በኢትዮጵያ ያሉ ነባር የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ከዚህ ግፊት ጋር ተያይዞ ከገበያ እንዳይወጡ ማድረግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ያተኩራል።
ዶ/ር ያሬድ በኢትዮጵያ የሚገኙ 18 የኢንሹራንስ ኩባንያዎችን መነሻ በማድረግ ባከናወኑት ጥናት የሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ተለይተዋል፦
-በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ የኢንሹራንስ ዘርፍ ያለው የዲጂታላይዜሽን አተገባበር እጅግ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
-ደንበኞች በባንክና በቴሌኮም ዘርፎች ባላቸው ልምድ ምክንያት ለዲጂታል አገልግሎት ዝግጁ ቢሆኑም፣ የኢንሹራንስ ዘርፉ ግን ይህንን ፍላጎት ለማሟላት ወደ ኋላ ቀርቷል።
-የደንበኞችን ታማኝነት ለማረጋገጥ መጀመሪያ አገልግሎቱ ደንበኛውን ማርካት ይኖርበታል፤ ይህ ደግሞ ያለ ዲጂታላይዜሽን የማይታሰብ መሆኑ ተገልጿል።
የኢንሹራንስ ኩባንያዎች የደንበኞችን ፍላጎት መሠረት ያደረገ፣ ለአጠቃቀም ቀላልና እምነት የሚጣልበት የዲጂታል አገልግሎት በአስቸኳይ ወደ ሥራ ሊያስገቡ እንደሚገባ በጥናቱ ተመልክቷል። ይህም ኩባንያዎቹ ያላቸውን ደንበኞች ይዘው እንዲቆዩና አዳዲስ ገበያዎችን እንዲቆጣጠሩ ይረዳቸዋል።
ዶ/ር ያሬድ አክለውም ኩባንያዎች ገበያቸውንና ደንበኞቻቸውን ሳያጡ በአስቸኳይ ዲጂታላይዜሽንን መተግበር አለባቸው፤ ምክንያቱም ደንበኛው ቀድሞ ዝግጁ ሆኖ እየጠበቀ ነው ብለዋል።
📸 ከበደ መክብብ
Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu



Source: GetuTemesgen









No comments yet.