በወላይታ ዞን በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የ4 ሰዎች ህይወት አለፈ
በወላይታ ዞን ዳሞት ጋሌ ወረዳ ሚያዝያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በጣለዉ ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በዳሞታ ተራራ ግርጌ ባሉ በወሽ ጋሌ እና በኮናሳ ፑላሳ ቀበሌዎች ነው አደጋው ደርሷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉን እና የሟቾች ቁጥር ከዚህ ከፍ ሊል ይችላል ሲሉ ተናግረዋል።
የዞኑ መንግሥት ተጎጂዎች ጎን በመቆም በዘላቂነት የመደገፍና የማቋቋም ሥራ ከወረዳው መንግሥት ጋር ለመሥራት ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
የዝናብ ሁኔታው ከመደበኛ በላይ የመጨመር አዝማሚያ ሊኖር ስለሚችል በዞኑ በካዎ ኮይሻ፣ ኪንዶ ኮይሻ፣ ኪንዶ ዲዳዬ፣ ድጉና ፋንጎ እና አበላ አባያ እንዲሁም ሌሎችም አካባቢዎች የመሬት መንሸራተት፣ ናዳ እና የወንዝ ሙላት ሊያጋጥም ስለሚችል ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል ተብሏል።
@seledadotio
@seledadotio
በወላይታ ዞን ዳሞት ጋሌ ወረዳ ሚያዝያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በጣለዉ ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በዳሞታ ተራራ ግርጌ ባሉ በወሽ ጋሌ እና በኮናሳ ፑላሳ ቀበሌዎች ነው አደጋው ደርሷል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉን እና የሟቾች ቁጥር ከዚህ ከፍ ሊል ይችላል ሲሉ ተናግረዋል።
የዞኑ መንግሥት ተጎጂዎች ጎን በመቆም በዘላቂነት የመደገፍና የማቋቋም ሥራ ከወረዳው መንግሥት ጋር ለመሥራት ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
የዝናብ ሁኔታው ከመደበኛ በላይ የመጨመር አዝማሚያ ሊኖር ስለሚችል በዞኑ በካዎ ኮይሻ፣ ኪንዶ ኮይሻ፣ ኪንዶ ዲዳዬ፣ ድጉና ፋንጎ እና አበላ አባያ እንዲሁም ሌሎችም አካባቢዎች የመሬት መንሸራተት፣ ናዳ እና የወንዝ ሙላት ሊያጋጥም ስለሚችል ጥንቃቄ ሊያደርጉ ይገባል ተብሏል።
@seledadotio
@seledadotio
Related Posts
- Advertisement -









No comments yet.