#Ethiopia | የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመንገደኞች አውሮፕላን ዛሬ ጧት ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ወደ መቐለ ከበረረ በኋላ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሳያርፍ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ።
አውሮፕላኑ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ማረፍ ያልቻለው፣ ከአውሮፕላን ማረፊያው የኮሚንኬሽን መሳሪያ ብልሽት ጋር በተያያዘ መኾኑን የአየር መንገዱ ሃላፊዎች እንደነገሩት ጠቅሶ የዘገበው ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ነው።
ኾኖም ከሰዓታት በኋላ የኮምንኬሽን መሳሪያው ብልሽት በመስተካከሉ አውሮፕላኑ ወደ መቐለ መጓዙን እንደተረዳ ምንጩ ጠቅሷል።
Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Source: GetuTemesgen









No comments yet.