በምርጫ ምልክት ላይ ጉዳት ያደረሰው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

- Advertisement -
Sidebar AD


‎በወላይታ ዞን ባይራ ኮይሻ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ የምርጫ ምልክት የሆነውን የ”ስንዴ ነዶ” ባነር ቀድዶ የጣለው ተከሳሽ በ5 ወር ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተወሰነበት።

‎ተከሳሽ አቶ በላቸው ባሳ በቀን 06/09/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 5:00 ገደማ በባይራ ኮይሻ ወረዳ “ጠካቻ ቀጠና 1” ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተሰቅሎ የነበረን የፓርቲውን የምርጫ ቅስቀሳ ባነር ቀድዶ በመጣል ለማምለጥ ሲሞክር በአካባቢው በነበሩ ሰዎች እጅ ከፍንጅ ተይዟል።

‎በወረዳው ፖሊስ ምርመራው በአስቸኳይ ተጠናቅቆ የቀረበለት ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሰረተ ሲሆን ተከሳሹ በ2011 ዓ.ም የወጣውን የኢትዮጵያ የምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162 አንቀጽ 158ን በመጣስ ወንጀል መፈጸሙን የሚያስረዱ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል።

‎ተከሳሹ የቀረበበትን የጥፋተኝነት ክስ አምኖ በችሎት ቃሉን ሰጥቷል።
‎የባይራ ኮይሻ ወረዳ ፍርድ ቤት መዝገቡን መርምሮ ድርጊቱ መፈፀሙን በማረጋገጡ ተከሳሹን የሚያርምና ሌሎችም ተመሳሳይ ድርጊት እንዳይፈጽሙ የሚያስተምር መሆን አለበት በማለት ተከሳሹ በ5 ወር እስራት እንዲቀጣ ወስኗል።

ምንጭ:- የወላይታ ዞን ፍትህ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ክፍል




Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: