#Ethiopia | የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በቅርቡ ባደረገው የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ (Mobile Banking App) ማሻሻያ ምክንያት በተወሰኑ ደንበኞች ላይ የአገልግሎት መስተጓጎል ማጋጠሙን ጠቅሶ፣ ችግሩን በአፋጣኝ ለመፍታት ርብርብ እያደረገ መሆኑን ገለጸ።
ባንኩ ለአገልግሎት ምቹና በርካታ አዳዲስ አማራጮችን ያካተተ የተሻሻለ መተግበሪያ ይፋ ማድረጉን ተከትሎ፣ በርካታ ደንበኞች እየተጠቀሙበት ቢሆንም፣ አዲስ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በአንዳንድ ተጠቃሚዎች ላይ መስተጓጎል መታየቱን አስታውቋል።
ባንኩ ለተፈጠረው መስተጓጎል ይቅርታ የጠየቀ ሲሆን፣ ችግሩ ሙሉ በሙሉ ተፈቶ ሲጠናቀቅ ለደንበኞቹ በይፋ እንደሚያሳውቅ ገልጿል።
ከተሻሻለው መተግበሪያ ጋር በተያያዘ ችግር ያጋጠማቸው ደንበኞች በሚከተሉት አማራጮች እገዛ እና ድጋፍ ማግኘት እንደሚችሉ ባንኩ ጠቁሟል፡
በነፃ የጥሪ ማዕከል: ወደ 951 በመደወል፣
በዲጂታል አማራጭ: በባንኩ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾች መልዕክት በመላክ፣
በቀጥታ ሊንክ: ባንኩ ባዘጋጀው የድጋፍ መስጫ ማስፈንጠሪያ (Link) በመጠቀም።
https://chat.whatsapp.com/BFR1h7SrAti091qznFEP4u
Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#የኢትዮጵያንግድባንክ #CBE
#ዲጂታልባንኪንግ #የሞባይልባንኪንግ #የደንበኞችአገልግሎት #የቴክኖሎጂማሻሻያ
Source: GetuTemesgen








No comments yet.