አምስቱ የምርጫ ክልሎቹ በሶማሌ ክልል የሚገኙ መሆናቸዉን ቦርዱ ይፋ እያደረገ ባለዉ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዉጤት ማሳወቂያ መርሃ ግብር ላይ ተገልፆል።
ሀማሬ፥ ዳራቶሬ፥ ሀርገሌ፥ ባቱ ዝዋይ፥ ቤጊ፥ አርሆሳ፥ ጨንቻ፥ ሶሮ 1፥ ጠንባሮ ፥ ሀደካላ፥ ሀደካለ ምርጫ ክልሎች የድጋሜ ምርጫ ይደረግባቸዋል ተብሏል።
በማእከላዊ ኢትዮጵያ ሶሬ1 እና ጠምባሮ ምርጫ ክልሎች ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤት የድጋሜ ምርጫ ይደረግላቸዋል።
ሀርገሌ ፥,ዳሮር፥ ሀደካላ ፥ ሀማሬ እና ዳራቶሬ የተባሉ በሶማሌ ክልል የሚገኙ የምርጫ ክልሎች የድጋሜ ምርጫ ያደርጋሉ።
ባቱ ዝዋይ እና ቤጌ ምርጫ ክልሎች በኦሮሚያ ክልል ለህዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክርቤት የድጋሜ ምረጫ የሚደረግበት ይሆናል ተብሏል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ጨንቻ ምርጫ ክልል ለክልል ምክርቤት የድጋሜ ምርጫ ይካሄዳል።
ዘገባው የኢትዮ ኤፍ ኤም ነው!
Source: FastMereja









No comments yet.