የሲ ኤም ሲ ተክለሃይማኖት ምእመናን ትናንት ማታ ታሪክ ሠርተዋል፤ ዛሬም ተቀጣጥረዋል

- Advertisement -
Sidebar AD

አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖትን ከልጅነት እሰከ እረፍት የተራዳቸው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው። እኛንም በሕይዎታችን ይራዳን።

ተክለሃይማኖት ፀሐይ
ነፍሴን አደራ በሰማይ ብለን የዘመርንለት ኢትዮጵያዊው ጻድቅ ሐዲስ ሐዋርያ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ሲ ኤም ሲ ላይ እንደ ፀሐይ እያበራ ነው።

መልእክት ከሲ ኤም ሲ አቡነ ተክለሃይማኖት የአባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ወዳጆች እንኳን ደስ አላችሁ

አዲስአበባ ላይ በግዝፈቱ የመጀሪያው በትክል ሁለተኛው በአባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ስም ቤተክርስቲያን እየታነፀ ነው። የት ነው ከላችሁ ከፀሐይ ሪል እስቴት ከፍ ብሎ ተራራው አናት ላይ በከፍታ ተገማሽሮ ይገኛል።

ይኽ መቅደስ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በርቀት እና በጊዜ እጥረት ምክንያት መሔድ ለማይችሉ ኦርቶዶክሳውያን የጻድቁን በረከት እዚሁ አዲስአበባ እንዲያገኙ ታስቦ እየተገነባ ያለ ቤተክርስቲያን ነው።

ጸበሉ ፈዋሸ ነው። የሰንበት ት/ቤቱ አገልግሎት ልዩ ነው። የመቅደሱ አገልግሎት ሰማያዊ ነው። አብነት ት/ቤቱም በመስፋፋት ላይ ነው።

ሰኔ 13 እና 14ም ልዩ የእራት እና የቀጥታ ሥርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐግብር ተዘጋጅቷል። ከምሽቱ 1፡00 ጀምሮ በኦርቶዶክሳውያን ቲክታከሮች እኒ ዩቱበሮች ተከታተሉ።

በሥር በተቀመጡት ስልኮች እየደወላችሁ ከጎናችን ቁሙ።

ለበለጠ መረጃ
0911145824
0911232741
0911418810

ደብሩን ለማገዝ እነዚህን አካውንቶች ተጠቀሙ
1000392187476 ንግድ
0096127311701 አሐዱ


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: