655 ሚሊዮን ሰዎች አሁንም የኤሌክትሪክ አገልግሎት የላቸውም – የተባበሩት መንግስታት ሪፖርት

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | በ2026 የወጣው የተባበሩት መንግስታት አዲስ ሪፖርት እንደሚያሳየው፣ በዓለም ዙሪያ 655 ሚሊዮን ሰዎች አሁንም የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሳያገኙ በጨለማ ውስጥ ይኖራሉ። ከእነዚህ ውስጥ ከ560 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት በሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ይገኛሉ።

ሪፖርቱ በተጨማሪ ወደ 2 ቢሊዮን የሚጠጉ ሰዎች አሁንም ለጤና ጎጂ የሆኑ የማብሰያ ነዳጆችን እና ቁሳቁሶችን እንደሚጠቀሙ ገልጿል። ይህም በየዓመቱ 3 ሚሊዮን ሰዎችን ለሚገድለው የቤት ውስጥ የአየር ብክለት ዋነኛ መንስኤ መሆኑን አመልክቷል።

በሌላ በኩል የታዳሽ ኃይል አጠቃቀም በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ30 በመቶ በላይ የኤሌክትሪክ ፍጆታን ቢሸፍንም፣ በበለጸጉና በዝቅተኛ ገቢ ሀገራት መካከል ያለው የኃይል አቅርቦት ልዩነት አሁንም እጅግ ሰፊ መሆኑን ሪፖርቱ ገልጿል።

የተባበሩት መንግስታት በ2030 ለሁሉም ሰው ተመጣጣኝና ዘመናዊ የኃይል አገልግሎት ለማዳረስ የአሁኑ የኤሌክትሪክ ዝርጋታ ፍጥነት ቢያንስ በሶስት እጥፍ መጨመር እንዳለበት አሳስቧል። በተለይም በታዳጊ ሀገራት ያለው የፋይናንስ እጥረትና የዓለም አቀፍ ድጋፍ መቀነስ ካልተፈታ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ከኃይል አገልግሎት ውጪ ሆነው እንደሚቀሩ ሪፖርቱ አስጠንቅቋል።


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1