በደቡብ ወሎ ገዳም በተፈጸመው ጥቃት ፓትርያርኩ ተጠያቂዎች ለፍትሕ እንዲቀርቡ ጠየቁ​ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በደቡብ ወሎ ሀ…

- Advertisement -
Sidebar AD
በደቡብ ወሎ ገዳም በተፈጸመው ጥቃት ፓትርያርኩ ተጠያቂዎች ለፍትሕ እንዲቀርቡ ጠየቁ
​ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በቦረና ወረዳ በግዮን አባይ ገዳም ላይ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. በተፈጸመው ጥቃት ጥብቅ መግለጫ አወጡ።
​በጥቃቱ የመነኮሳይያት ሕይወት ማለፉን፣ በርካቶች መቁሰላቸውንና በንዋየ ቅድሳቱ ላይ ውድመት መድረሱን የገለጹት ቅዱስነታቸው፣ በዚሁ ዕለት በሀድያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የአምልኮ ሥፍራ መፍረሱንና በምእመናን ላይ ጥቃት መድረሱን አውግዘዋል።
​መንፈሳዊ ማዕከላት የሰላምና የእሴት ምንጭ በመሆናቸው፣ ገዳማትን መጠበቅ የባለሥልጣናትና የሕግ አስከባሪዎች ኃላፊነት መሆኑን አስገንዝበዋል።
አሰቃቂውን ድርጊት የፈጸሙ አካላት በአስቸኳይ ለፍትሕ እንዲቀርቡ፣ ለሌሎች ገዳማት ጥበቃ እንዲደረግና ለተጎዱት ድጋፍ እንዲያገኝ ጥሪ አቅርበዋል።
​በመጨረሻም ሕዝበ ክርስቲያኑ ከተጎዱት ጎን እንዲቆም አሳስበው፣ ለተበደሉት ፍትሕንና ለሀገሪቱ ሰላምን ተመኝተዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: