የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት እስከ ነሀሴ 30 /2018 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት እየወሰደ ባለው እርምጃ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ መወስኑን ተከትሎ የውል እድሳት ምዝገባም ከ ሐምሌ 1 / 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ይህንን ተከትሎ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ የውል እድሳት ምዝገባ ግዜ እስከ እስከ ሀምሌ 30 /2018 ዓ.ም የነበረው እስከ ነሀሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።
የውል እድሳት ግዜው በህብረተሰቡ ጥያቄ መስረት የተራዘመ ሲሆን ነዋሪው ያለምንም መጨናነቅ እንዲዋዋል ታሳቢ ያደረገ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል።
ህብረተሰቡ በሁሉም ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት ፤ በየወረዳው በተዘጋጁ የውል ቦታዎች እና በሁሉም ክፍለ ከተማ አዲስ መሶብ አስፈላጊውን መረጃ ይዞ በመገኘት አገልግሎቱን ማግኘት የሚቻል መሆኑን ቢሮው በድጋሚ ያሳውቃል፡፡
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ
Source: Yeneta Tube









No comments yet.