ግብፅ፣ ሱዳን፣ ጂቡቲ፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ በሳዑዲ አረቢያ የሚመራውን ስምንት አገራትን ያካተተ የቀይ ባህርና የኤደን ባህረ ሰላጤ አዲስ የደህንነት ጥምረት ተቀላቀሉ፡፡
ሳዑዲ አረቢያ ስምንት በቀይ ባህር እና በኤደን ባህረ ሰላጤ የሚገኙ ሀገራትን በማስተባበር አዲስ ተጨማሪ የባህር ላይ የደህንነት ጥምረት አዋቅራለች።
ከእነዚህ ስምንት ሀገራት መካከል አምስቱ ሀገራት ግብፅ፣ ሱዳን፣ ጂቡቲ፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ ናቸው።
የታቀደው ህብረት ሳዑዲ አረቢያን፣ ዮርዳኖስን፣ የመንን እና አምስቱን የአፍሪካ ሀገራት ያካተተ ነው።
የሳዑዲ አረቢያ የመከላከያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ ጥምረቱ ዓላማው በቀይ ባህር ላይ በሚያዋስኑ ሀገራት መካከል ያለውን ቅንጅት ማጠናከር እና ዓለም አቀፍ የባህር ላይ መስመሮችን፣ የንግድና የኃይል ማጓጓዣ መንገዶችን እንዲሁም የጋራ የባህር ላይ ጥቅሞችን መጠበቅ መሆኑን አስታውቋል።
ጥምረቱ የተመሰረተው በቀጠናው ውጥረቶች እና በንግድ መርከቦች ላይ የሚደርሱ መስተጓጎሎች እየጨመሩ የመጡበት ወቅት ላይ ነው።
@Seledadotio
@Seledadotio
ሳዑዲ አረቢያ ስምንት በቀይ ባህር እና በኤደን ባህረ ሰላጤ የሚገኙ ሀገራትን በማስተባበር አዲስ ተጨማሪ የባህር ላይ የደህንነት ጥምረት አዋቅራለች።
ከእነዚህ ስምንት ሀገራት መካከል አምስቱ ሀገራት ግብፅ፣ ሱዳን፣ ጂቡቲ፣ ኤርትራ እና ሶማሊያ ናቸው።
የታቀደው ህብረት ሳዑዲ አረቢያን፣ ዮርዳኖስን፣ የመንን እና አምስቱን የአፍሪካ ሀገራት ያካተተ ነው።
የሳዑዲ አረቢያ የመከላከያ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ ጥምረቱ ዓላማው በቀይ ባህር ላይ በሚያዋስኑ ሀገራት መካከል ያለውን ቅንጅት ማጠናከር እና ዓለም አቀፍ የባህር ላይ መስመሮችን፣ የንግድና የኃይል ማጓጓዣ መንገዶችን እንዲሁም የጋራ የባህር ላይ ጥቅሞችን መጠበቅ መሆኑን አስታውቋል።
ጥምረቱ የተመሰረተው በቀጠናው ውጥረቶች እና በንግድ መርከቦች ላይ የሚደርሱ መስተጓጎሎች እየጨመሩ የመጡበት ወቅት ላይ ነው።
@Seledadotio
@Seledadotio
- Advertisement -









No comments yet.