በአዲስአበባ ጉዳይ ተወሰነ
አከራካሪ የነበረው የአዲስ አበባ ጉዳይ ስምምነት እንደተደረሰበት ተገለጸ
በተመካካሪዎች ዘንድ በሰፊው አከራካሪ ከነበሩ አጀንዳዎች መካከል የፌደራል ከተሞች፡- የአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ጉዳይ ዋነኛው ሲሆን፣ በዛሬው የምክክር ውሎ በአጀንዳው ላይ ስምምነት ላይ እንደተደረሰ ተገልጿል።
ከሐምሌ 8/2018 ዓ.ም. ጀምሮ በይፋ በተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 4 ሺህ ተመካካሪዎች በተመረጡ 8 አጀንዳዎች ላይ ሲመክሩ መቆየታቸው ይታወቃል።
በዛሬው የምክክር ጉባኤ ውሎ በተመካካሪዎች ዘንድ በሰፊው አከራካሪ የነበረው የፌደራል ከተሞች፡- የአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ጉዳይ አጀንዳ ስምምነት እንደተደረሰበት ታውቋል።
በዚህ መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ የፌደራል እና የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ እንድትሆን 500 አባላት ያሉት የተመካካሪዎች ቡድን ተስማምተዋል።
ልዩ ጥቅምን በተመለከተ ዝርዝር ጉዳዮች በቀጣይ በሰፊው እንደሚመከርባቸው ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ጉዳይ በተመካካሪዎች ዘንድ በሁለት ጎራ፤ «የኦሮሚያ ክልል አካል እና ዋና መቀመጫ ትሁን» በሚል እና «የፌደራል ከተማ ዋና መቀመጫ ትሁን» በሚል በተመካካሪዎች ዘንድ ለቀናት ሲያጨቃጭቅ መቆየቱ የሚታወስ ነው።
@Seledadotio
@Seledadotio
አከራካሪ የነበረው የአዲስ አበባ ጉዳይ ስምምነት እንደተደረሰበት ተገለጸ
በተመካካሪዎች ዘንድ በሰፊው አከራካሪ ከነበሩ አጀንዳዎች መካከል የፌደራል ከተሞች፡- የአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ጉዳይ ዋነኛው ሲሆን፣ በዛሬው የምክክር ውሎ በአጀንዳው ላይ ስምምነት ላይ እንደተደረሰ ተገልጿል።
ከሐምሌ 8/2018 ዓ.ም. ጀምሮ በይፋ በተጀመረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 4 ሺህ ተመካካሪዎች በተመረጡ 8 አጀንዳዎች ላይ ሲመክሩ መቆየታቸው ይታወቃል።
በዛሬው የምክክር ጉባኤ ውሎ በተመካካሪዎች ዘንድ በሰፊው አከራካሪ የነበረው የፌደራል ከተሞች፡- የአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ጉዳይ አጀንዳ ስምምነት እንደተደረሰበት ታውቋል።
በዚህ መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ የፌደራል እና የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ እንድትሆን 500 አባላት ያሉት የተመካካሪዎች ቡድን ተስማምተዋል።
ልዩ ጥቅምን በተመለከተ ዝርዝር ጉዳዮች በቀጣይ በሰፊው እንደሚመከርባቸው ተገልጿል።
የአዲስ አበባ ጉዳይ በተመካካሪዎች ዘንድ በሁለት ጎራ፤ «የኦሮሚያ ክልል አካል እና ዋና መቀመጫ ትሁን» በሚል እና «የፌደራል ከተማ ዋና መቀመጫ ትሁን» በሚል በተመካካሪዎች ዘንድ ለቀናት ሲያጨቃጭቅ መቆየቱ የሚታወስ ነው።
@Seledadotio
@Seledadotio









No comments yet.