#Ethiopia | የኢትዮጵያ አየር መንገድ በውጭ ሀገራት ከትኬት ሽያጭ ያገኘው 90 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ወደ ሀገር ውስጥ ሳይዘወር መቆየቱን የድርጅቱ የንግድ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ለማ ያደቻ ገለጹ።
ከተያዘው ገንዘብ ውስጥ አጋማሹ ማለትም 45 ሚሊዮን ዶላር በሩሲያ ላይ በተጣሉ የፋይናንስ ማዕቀቦች ሳቢያ በዚያው በሩሲያ የቆየ ሲሆን ቀሪው 45 ሚሊዮን ዶላር ደግሞ እንደ አንጎላ እና ሞዛምቢክ ባሉ ሀገራት ባጋጠመ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ምክንያት መዘግየቱ ተብራርቷል።
አየር መንገዱ ወደ ሞስኮ የሚያደርገውን የዕለት ተዕለት በረራ በመቀጠል የሚሰበስበውን ገቢ ለአካባቢው ወጪዎች ቢጠቀምበትም የባንክ ማዕቀቡ የተጣራ ትርፉን ለማስወጣት እንቅፋት በመሆኑ ችግሩን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት እየሰራ ይገኛል።
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በነሐሴ ወር 2018 ዓ.ም በጡረታ ይገለላሉ ተብሎ ይጠበቅ የነበረ ቢሆንም የአገልግሎት ዘመናቸው ለተጨማሪ ጊዜ እንዲራዘም ተወስኗል።
የዳይሬክተሮች ቦርድ ያስተላለፈው ይህ ውሳኔ አየር መንገዱ እያካሄደ ያለውን የ12.6 ቢሊዮን ዶላር የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታንና የትራንስፖርት አቅም ማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን በተረጋጋ አመራር ለማስቀጠል ያለመ ነው ተብሏል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Source: GetuTemesgen









No comments yet.