በመቀሌ ከተማ በሁለት የተለያዩ ቦታዎች በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ህፃናትን ጨምሮ 13 ሰዎች ቆስለው አይደር ሆስፒታል ገቡ። የመጀ…

- Advertisement -
Sidebar AD
በመቀሌ ከተማ በሁለት የተለያዩ ቦታዎች በተፈጸመ የድሮን ጥቃት ህፃናትን ጨምሮ 13 ሰዎች ቆስለው አይደር ሆስፒታል ገቡ።
የመጀመሪያው ጥቃት በሐወልቲ ክፍለ ከተማ፣ ሞሞና ቀበሌ፣ በቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን አቅራቢያ የመኖሪያ ቤቶችን ኢላማ ያደረገ ነበር ተብሏል።
አይደር ሆስፒታል እንዳስታወቀው፤ ዛሬ ጠዋት 5:30 ገደማ አዋቂዎችንና ህፃናትን ያካተቱ 13 ተጎጂዎችን ተቀብሎ አስቸኳይ ቀዶ ህክምና እያደረገላቸው ይገኛል።
ሁለተኛው ጥቃት ደግሞ በመቀሌ ኩሃ አካባቢ መፈጸሙን ነዋሪዎች ለአዲስ ስታንዳርድ አረጋግጠዋል።
በጥቃቱ ስለደረሰው የንብረትና የሰው ጉዳት ዝርዝር መረጃዎች እየወጡ ነው።
መቀሌ አሁንም በከፍተኛ ስጋት ላይ ትገኛለች።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: