የኢትዮጵያ ብር ከአሜሪካ ዶላር አንጻር የመመንዘር አቅሙ በታሪክ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ መድረሱና ሀገሪቱ ያጋጠማትን የውጭ ምንዛሬ …

- Advertisement -
Sidebar AD
የኢትዮጵያ ብር ከአሜሪካ ዶላር አንጻር የመመንዘር አቅሙ በታሪክ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ መድረሱና ሀገሪቱ ያጋጠማትን የውጭ ምንዛሬ እጥረት ለማረጋጋት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 2.2 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ማድረጉ ተገለፀ።
ብሉምበርግ የዜና ምንጭ ባወጣው ዘገባ መሰረት፣ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሬ ገበያ ለማረጋጋትና የብርን እሴት ለመደገፍ ብሔራዊ ባንኩ ከፍተኛ መጠን ያለው የዶላር ክምችት ስራ ላይ ያዋለ ቢሆንም የብር የመግዛት አቅም ግን ታሪካዊ ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ወርዷል።
ይህ በውጭ ምንዛሬ ገበያው ላይ የታየው ተጽዕኖ በሀገሪቱ ምጣኔ ሀብትና በዜጎች የእለት ተእለት የኑሮ ውድነት ላይ ተጨማሪ ጫና ይፈጥራል የሚል ስጋት የፈጠረ ሲሆን፣ የብሔራዊ ባንክ ውሳኔና በውጭ ምንዛሬ ገበያው ላይ የሚወሰዱ ቀጣይ እርምጃዎች የአለምአቀፉን የፋይናንስ ማህበረሰብ ትኩረት ስበዋል።
@Seledadotio
@Seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1

You might want to listen to: