ኢትዮጵያ ያለባትን የ1 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ዕዳ ለመክፈል ከአበዳሪዎቿ ጋር ስምምነት ላይ ደረሰች!
ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የግል አበዳሪዎች ተበድራው የነበረውን 1 ቢሊዮን ዶላር (ዩሮቦንድ) በወቅቱ መክፈል አቅቷት የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ዕዳውን የምታቀልበት የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ኢትዮጵያ ከነበረባት 1 ቢሊዮን ዶላር ላይ የ12% ቅናሽ የተደረገላት ሲሆን በዚህ መሰረት የምትከፍለው ዕዳ ወደ 880 ሚሊዮን ዶላር ዝቅ ብሏል።
ይህንን 880 ሚሊዮን ዶላር እስከ 2029 ድረስ በ6.15% ወለድ በየደረጃው እንድትከፍል ጊዜ የተሰጣት ሲሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት ሳትከፍል ያሳለፈችውን 99.4 ሚሊዮን ዶላር የወለድ ዕዳ ትከፍላለች።
ስምምነቱ ወደፊት ኢትዮጵያ ብድር ባስፈለጋት ጊዜ እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ድረስ በድጋሚ የመበደር መብት ወይም ዕድልን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) እና ዋናዎቹ አበዳሪ ሀገራት (ቻይና እና ፈረንሳይ) ስምምነቱን የደገፉ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ገፅታ የሚያሻሽልና ተጨማሪ የውጭ ብድርና 1እርዳታ በቀላሉ እንድታገኝ በር የሚከፍት በመሆኑ .በገበያው ላይ ትልቅ ተስፋን ጥሏል።
በየአብሥራ ተፈራ
@Seledadotio
@Seledadotio
ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የግል አበዳሪዎች ተበድራው የነበረውን 1 ቢሊዮን ዶላር (ዩሮቦንድ) በወቅቱ መክፈል አቅቷት የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ዕዳውን የምታቀልበት የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሷን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።
ኢትዮጵያ ከነበረባት 1 ቢሊዮን ዶላር ላይ የ12% ቅናሽ የተደረገላት ሲሆን በዚህ መሰረት የምትከፍለው ዕዳ ወደ 880 ሚሊዮን ዶላር ዝቅ ብሏል።
ይህንን 880 ሚሊዮን ዶላር እስከ 2029 ድረስ በ6.15% ወለድ በየደረጃው እንድትከፍል ጊዜ የተሰጣት ሲሆን ባለፉት ሁለት ዓመታት ሳትከፍል ያሳለፈችውን 99.4 ሚሊዮን ዶላር የወለድ ዕዳ ትከፍላለች።
ስምምነቱ ወደፊት ኢትዮጵያ ብድር ባስፈለጋት ጊዜ እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ድረስ በድጋሚ የመበደር መብት ወይም ዕድልን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) እና ዋናዎቹ አበዳሪ ሀገራት (ቻይና እና ፈረንሳይ) ስምምነቱን የደገፉ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ገፅታ የሚያሻሽልና ተጨማሪ የውጭ ብድርና 1እርዳታ በቀላሉ እንድታገኝ በር የሚከፍት በመሆኑ .በገበያው ላይ ትልቅ ተስፋን ጥሏል።
በየአብሥራ ተፈራ
@Seledadotio
@Seledadotio
Related Posts
- Advertisement -









No comments yet.