በሴቶች 3000 ሜትር ኢትዮጵያ ወርቅና ብር ሜዳሊያ አገኘች!

- Advertisement -
Sidebar AD

እንኳን ደስ አለን !

በአሜሪካ ኦሪገን እየተካሄደ ባለው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሴቶች 3000 ሜትር ውድድር አትሌቶቻችን ተከታትሎ በመግባት ተጨማሪ ሜዳልያዎች ለኢትዮጵያ አስገኝቷል

አትሌት ዮርዳኖስ ፅጋብ በ8:43.65 በመግባት የግል ምርጥ ሰዓቷን በማስመዝገብ በአንደኝነት አሸንፋለች ።

አትሌት ሽቶ ጉሚ በ8:45.06 በመግባት የብር ሜዳሊያ አስገኝታለች።

ይህም በ3000 ሜትር ውድድር ወርቅና ብር በኢትዮጵያ እጅ እንዲገባ ያደረገ አስደናቂ የስኬት ጊዜ ሆኗል።

አትሌት ሽቶ ጉሚ በዚህ ሻምፒዮና በ5000 ሜትር ለኢትዮጵያ የብር ሜዳሊያ ማስገኘቷም ይታወሳል።

በሌሎች ውድድሮች በሴቶች 800 ሜትር የፍፃሜ ውድድር አትሌት ሀብታም ገበየሁ በ2:03.99 አራተኛ ስትወጣ፣ አትሌት ደራርቱ ሽብሩ በ2:04.81 ሰባተኛ በመሆን ውድድራቸውን አጠናቀዋል።

በወንዶች 5000 ሜትር እርምጃ ፍፃሜ የተሳተፈው አትሌት ነገሮ አዱኛ በ20:22.82 የግል ምርጥ ሰዓቱን በማስመዝገብ 19ኛ ሆኖ ውድድሩን አጠናቋል።

ሻምፒዮናው ዛሬ ፍፃሜውን የሚያገኝ ይሆናል።




Source: FastMereja

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1