ትራምፕ ሌሶቶን “ማንም ሠምቷት የማያውቅ” ሀገር ማለታቸው “አስደንግጦኛል” ሲሉ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተናገሩ

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | “በዓለም ላይ በጣም ታዋቂ እና ልዩ ከሆኑ ሀገሮች አንዷ ሌሶቶ ናት። ፕሬዝዳንቱ እንዲሁም ቀሪው ዓለም ሌሴቶን መጥቶ እንዲጎበኝ በደስታ እጋብዛለሁ” ሲሉ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሌጆኔ ምፖትጆአኔ ተናግረዋል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ማክሰኞ ለአሜሪካ ኮንግረስ ባደረጉት ንግግር የውጭ እርዳታ ካቋረጡባቸው ሀገራት ውስጥ “ብዙ ገንዘብ የባከነባት” ያሏትን ሌሶቶ አንስተዋል። እንደ ትራምፕ ገለጻ በሌሶቶ የ LGBTQI+* መብቶችን ለማበረታት 8 ሚሊዮን ዶላር ተመድቦ ነበር።

ድጋፉ በመቋረጡ ምክንያት በተለይም በዩናይትድ ስቴትስ ፈንድ የሚደገፉት የሀገሪቱ የጤና እና ግብርና ዘርፎች ተፅዕኖ እንደደረሳባቸው ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ሀገሪቱ ራሷን በተሻለ መንገድ የምትችልባቸውን መንገዶች እያሳሰች እንደሆነም ነው ሚኒስትሩ ጨምረው የገለፁት።

*የኤልጂቢቲ እንቅስቃሴ ከባሕል ያፈነገጠ ጽንፈኛ ቡድን ተብሎ ሩሲያ ውስጥ ታግዷል።

#sputnik

ባሉበት ሆነው ትኩስ እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኝት ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ።

“””””””””””***””””””””””
ዩቲዩብ ገጽ: https://www.youtube.com/@getutemesgenet

ፌስቡክ ገጽ: https://web.facebook.com/getu26

ቴሌግራም ገጽ: https://t.me/getutemesgenet

ቲክቶክ ገጽ: https://www.tiktok.com/@getutemesgenet

ኢንስታግራም ገጽ: https://www.instagram.com/getutemesgenet

ኤክስ: https://x.com/getutemesgenet

አማርኛ ድረ-ገጽ: https://getutemesgen.et

ኢንግሊዘኛ ድረ-ገጽ: https://en.getutemesgen.et





Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: