​ትራምፕ የአሜሪካ ጦር ከጀርመን እንዲወጣ ፍላጎት ማሳየታቸው መነጋገሪያ ሆኗል​ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጀርመን የሚገኘውን …

- Advertisement -
Sidebar AD
​ትራምፕ የአሜሪካ ጦር ከጀርመን እንዲወጣ ፍላጎት ማሳየታቸው መነጋገሪያ ሆኗል
​ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጀርመን የሚገኘውን የአሜሪካ ጦር ለማስወጣት ማሰባቸውን መግለጻቸው በፔንታጎን እና በጀርመን ባለስልጣናት ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤን መፍጠሩን ፖሊቲኮ ዘግቧል።

የፔንታጎን (የመከላከያ ሚኒስቴር) ከፍተኛ መኮንኖች ስለ ጉዳዩ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰሙት ትራምፕ በ”ትሩዝ ሶሻል” ካሰፈሩት ጽሁፍ መሆኑ ተገልጿል።ይህ እቅድ በቅርቡ የፔንታጎን ባለሙያዎች በአውሮፓ ያለውን የጦር ኃይል መቀነስ እንደማይገባ ካቀረቡት የጥናት ውጤት ጋር የሚጋጭ ነው።
​የጀርመን ባለስልጣናት በነገሩ መገረማቸውን ገልጸው፣ የአሜሪካ ጦር መውጣት አሜሪካን ራሷን ለከፋ ድክመት እንደሚዳርጋት አስጠንቅቀዋል።በአሁኑ ወቅት ጀርመን ውስጥ ከ35,000 እስከ 40,000 የሚደርሱ የአሜሪካ ወታደሮች ይገኛሉ።
አሜሪካ በአሁኑ ወቅት ከኢራን ጋር በጦርነት ላይ ባለችበት ወቅት፣ በጀርመን የሚገኘውን ግዙፍ ወታደራዊ መሠረተ ልማት እና ኃይል በፍጥነት ለማስወጣት መሞከር እጅግ ውድ እና በሎጂስቲክስ ረገድ ፈታኝ እንደሚሆን ባለሙያዎች ይገልጻሉ
@seledadotio
@seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1