ትራምፕ ከኢራን ጦርነት መጠናቀቅ በሗላ ቀጣይዋ ተረኛ ኩባ ናት ሲል አስታውቋል።አዳሩን ለመገናኛ ብዙሀን መግለጫ የሰጠው ትራምፕ…

- Advertisement -
Sidebar AD
ትራምፕ ከኢራን ጦርነት መጠናቀቅ በሗላ ቀጣይዋ ተረኛ ኩባ ናት ሲል አስታውቋል።
አዳሩን ለመገናኛ ብዙሀን መግለጫ የሰጠው ትራምፕ የኢራን ጦርነቱ ተጠናቋል ካለ በሗላ የጦር ጄት ተሸካሚ መርከቦቻችን ወደ ኩባ እየተጓዙ ነው ብሏል። እናም ኩባን በአጭር ጊዜ ውስጥ እንቆጣጠራታለን ሲል ዝቷል።
” ኩባ ችግር ያለባት ሀገር ናት ስለዚህ ቶሎ እንጨርሳታለን። እኔ ነገሮችን መጨረስ እወዳለሁ” በማለት የኩባ ጉዳይ ቶሎ እንደሚጠናቀቅ አስታውቋል።
ትራምፕ ኩባን ለማንበርከክ ከአለም ግዙፉ የጦር ጄት ተሸካሚ መርከብ አብረሀም ሊንከን እንደሚሰማራ ገልጿል።
ኩባ የሰብአዊነትና የነፃነት ተምሳሌት የሆነች ሀገር ስትሆን በአሁኑ ሰአት በአሜሪካ ሁለገብ ከበባና ማእቀብ ውስጥ ትገኛለች።
አሜሪካ በኢራን ከተሸነፈች በሗላ ወደ ደካማ ሀገራት ፊቷን አዙራለች።
ኩባ በበኩሏ የግዛቷን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ ከአሜሪካ ጋር እንደምትፋለም አስታውቃለች።የኩባው ፕሬዝዳንት ሚጉዌል ዲያዝ ካኔል እንደገለፁት “ኩባ ጦርነት ባትፈልግም ለሀገር ሉአላዊነት መላ ኩባዊያን ለመፋለም ዝግጁ ናቸው”
@seledadotio
@seledadotio

Source: SeledaPost

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom1