ተዋናይ ዳንኤል ታደሰ

- Advertisement -
Sidebar AD

የሁላችንም ትብብርና ድጋፍ ያስፈልገዋል

#Ethiopia | በበርካታ ዓለም አቀፍ ፊልሞችና ቀን ዘራፊ በተሰኘው የሀገር ውስጥ ፊልም ላይ የተወነው አንጋፋው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር በተዘጋጀ የሽልማት መርሃ ግብር ላይ ለጥበብ ያለውን ጥልቅ ክብር አሳይቷል።

ተዋናዩ ለረጅም ዓመታት በኦክስጅን ድጋፍ የሚተነፍስ ቢሆንም የፊልም ምርቃቱን ለመታደም ሲል ኦክስጅኑን አላቅቆ በመገኘት ሽልማቱን ተቀብሏል።

በወቅቱ የናፈቀውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር መድረክ በመሳም ለሙያው ያለውን ፍቅር የገለጸ ቢሆንም ፕሮግራሙ ሲጠናቀቅ ግን በገጠመው የትንፋሽ እጥረት ምክንያት ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ተወስዶ በህክምና ክትትል ላይ ይገኛል።

ይህ ለጥበብ ራሱን አሳልፎ የሰጠ ተዋናይ በህክምና ታግዞ ወደ ቀድሞ ጤንነቱ እንዲመለስ የሁላችንም ትብብርና ድጋፍ ያስፈልገዋል።

ዳንኤልን መርዳት ለምትፈልጉ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000522370456 ዳንኤል ታደሰ ብላችሁ ድጋፋችሁን ማድረስ ትችላላችሁ።

መረጃው ለደጋግ ኢትዮጵያውያን እንዲደርስ በማጋራት ተባበሩ።

በረከት ወረደ ማያ

#ethiopianfilm #artistdanieltadesse #help #art #cinema #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2