ማንችስተር ዩናይትድ ማይክል ካሪክን የሁለት ዓመት ውል በመስጠት የክለቡ ቋሚ አሰልጣኝ አድርጎ መሾሙን አረጋግጧል።
ሩበን አሞሪም በጥር ወር ከኃላፊነታቸው ከተሰናበቱ በኋላ የ44 ዓመቱ አሰልጣኝ በጊዜያዊነት ቦታውን ተረክቦ አስደናቂ ጉዞ በማድረግ ክለቡ በቻምፒዮንስ ሊግ ተሳታፊ የሚያደርገውን ቦታ እንዲያገኝ አስችሏል።
በኃላፊነት ከመራቸው 16 ጨዋታዎች ውስጥ 11ዱን አሸንፏል።
ለፕሪምየር ሊጉ የዓመቱ ምርጥ አሰልጣኝ ሽልማት ከታጩ ስድስት አሰልጣኞች ዝርዝር ውስጥ ተካትቷል።
ካሪክ በጥር በጊዜያዊነት ከተሾመበት ጊዜ ጀምሮ ዩናይትድ ካሰበሰበው 36 ነጥብ በላይ ያገኘ ሌላ የሊጉ ክለብ የለም።
Source: Yeneta Tube









No comments yet.