በዝዋይ ደሴት የሚኖሩት ታቦት ጠባቂዋ የ 107 ዓመት እናት ዐረፉ

- Advertisement -
Sidebar AD

ገሊላ ደሴት የሄደ ሁሉ የሚያገኛቸው ታላቋ ምልክት እናት፤

በዚች ዓለም 107 ዓመታት ሲኖሩ 87ቱን ዓመታት ብቻቸውን በገሊላ ደሴት ገዳምና ታቦቱን እየጠበቁ አሳለፉት። አዴ ኩሼ ጎንደር የዝዋይ (ባቱ) የገሊላ ደሴት ምልክት ናቸው።

የደሴቱ ሰዎች ወደ ከተማ መሬት ሲሄዱ፤ እርሳቸው ግን ከካህናተ-ሰማይ ታቦት ጋር መኖርን መረጡ

ምንም ባይኖራቸውም በሕይወታቸው ደስተኛ ሆነው የኖሩ ብርቱና ድንቅ እናት ናቸው። ሃይማኖት በምን መልኩ ሰውን እንደሚያኖር ምልክት ናቸው።

ዛሬ ግን ወደሚወዳቸው እግዚአብሔር እቅፍ እረፍት ወዳለበት ወደ ሀገራቸው የሰማይ ቤታቸው ሄደዋል።

እግዚአብሔር ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ያሳርፍልን



Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2