የፈረንሳይ መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዜጎቹ ወደትግራይ ክልል እንዳይሄዱ ማስጠንቀቂያ ሰጠ፡፡

- Advertisement -
Sidebar AD

ሚኒስትሩ ምሽቱን ባወጣው በዚህ የጉዞ ማስጠንቀቂያ በህወሀት መካከል የተፈጠረውን ሽኩቻ ጠቅሶ በተለይ ወደአዲግራትና ዋና ከተማዋ መቀሌ ፈረንሳዊያን ፈፅሞ እንዳይሄዱ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡

በትግራይ ክልል ውስጥ ያለው ሽኩቻ ወደጦር መሳሪያ ግጭት መለወጡን ጠቅሶም በዚያው የሚገኙ ፈረንሳዊያን በተቻለ ፍጥነት ክልሉን ለቀው እንዲወጡ ጥሪ አቅርቧል፡፡

በተጨማሪም በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ያለው ውጥረት የመጨመር ምልክቶች እየታዩበት መሆኑን የጠቀሰው ሚኒስትሩ በዚህ የተነሳ በአፋር ክልል ሰሜናዊ ክፍል አጋማሽ ድረስ ፈረንሳዊያን መሄድ እንደሌለባቸው አሳስቧል፡፡ በአፋር ክልል የሚገኘውን የአርታሌ እሳተ ጎመራ ለመጎብኘት እቅድ ያላቸው ፈረንሳዊያንም ፕሮግራማቸውን እንዲያራዝሙት ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡



Source: Yeneta Tube

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: