ኢትዮጵያውያን ከገቢያቸው 58.5 በመቶውን ለምግብ ፍጆታ እያዋሉ መሆኑ ተገለጸ

- Advertisement -
Sidebar AD

#Ethiopia | የዓለም ባንክ ይፋ ባደረገው አዲስ አህጉራዊ ሪፖርት፣ በኢትዮጵያ ያለውን የኑሮ ውድነት ጫና የሚያሳይ አሳሳቢ አኃዝ ይፋ አድርጓል። ሪፖርቱ እንደሚጠቁመው፣ ኢትዮጵያውያን ከአጠቃላይ ወጪያቸው ውስጥ ከ58.5 በመቶ በላይ የሚሆነውን ለምግብ ፍጆታ ብቻ ለማዋል ተገደዋል።

የዋጋ ንረቱ የከተማ ነዋሪዎችን ብቻ ሳይሆን፣ በገጠር የሚገኙ ዜጎችንም በከፍተኛ ሁኔታ እየፈተነ ይገኛል። የሸቀጦች ዋጋ መጨመር በገጠር ያለውን የኑሮ ሚዛን እያናጋው መሆኑ ተመልክቷል።

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ቀውስ የነዳጅ ዋጋን በመጨመር፣ በሀገር ውስጥ ያለውን የትራንስፖርትና የምርት ዋጋ ይበልጥ ሊያናረው እንደሚችል ባንኩ አስጠንቅቋል።

ይህ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ከምግብ ዋስትና ጋር ተዳምሮ የዜጎችን የመግዛት አቅም ይበልጥ ሊያዳክም እንደሚችል ተጠቁሟል።

ይህ መረጃ እንደሚያሳየው፣ የኑሮ ውድነቱ ከምግብ ፍጆታ አልፎ አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴው ላይ የራሱን ጫና ማሳረፉን ቀጥሏል።

Getu Temesgen – (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ebs #Ethiopia #Economy #WorldBank #Inflation #FoodSecurity #NewsUpdate #LeadThePlot #AddisAbaba #GlobalEconomy


Source: GetuTemesgen

Comments

No comments yet.

- Advertisement -
Advertisement post bottom2

You might want to listen to: