አዲስ የአውሮፕላን መለዋወጫ ፋብሪካ ሊመረቅ ነው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ ከብሔራዊ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዓለም አቀፉ የቦይንግ ኩባንያ ጋር በመተባበር የገነባው የኤሮስፔስ መለዋወጫዎች ማምረቻ ፋብሪካ መጠናቀቁንና በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ እንደሚመረቅ አስታውቀዋል። ይህ ግዙፍ ፋብሪካ ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ኢንዱስትሪ ያላትን አቅም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ሲሆን፣ በተለይም በዘርፉ በውጭ ሀገር ምርቶች ላይ ያለውን ጥገኝነት በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቀደም ሲል ለቦይንግ ኩባንያ የተለያዩ የአውሮፕላን መለዋወጫ ግብዓቶችን እያመረተ ማቅረብ መጀመሩ የሚታወስ ሲሆን፣ የአሁኑ ፋብሪካ መጠናቀቅ ደግሞ ሀገሪቱ በኤሮስፔስ ቴክኖሎጂ ያላትን ተወዳዳሪነት የሚያጎለብት ነው። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ ከአውሮፕላን ተጠቃሚነት ባለፈ ወደ አምራችነትና ላኪነት የተሸጋገረችበትን አዲስ ምዕራፍ የሚያበስር ታሪካዊ እርምጃ ሆኖ ተመዝግቧል።
@seledadotio
@seledadotio
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ ከብሔራዊ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዓለም አቀፉ የቦይንግ ኩባንያ ጋር በመተባበር የገነባው የኤሮስፔስ መለዋወጫዎች ማምረቻ ፋብሪካ መጠናቀቁንና በሚቀጥሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ እንደሚመረቅ አስታውቀዋል። ይህ ግዙፍ ፋብሪካ ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ኢንዱስትሪ ያላትን አቅም ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር ሲሆን፣ በተለይም በዘርፉ በውጭ ሀገር ምርቶች ላይ ያለውን ጥገኝነት በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስ ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቀደም ሲል ለቦይንግ ኩባንያ የተለያዩ የአውሮፕላን መለዋወጫ ግብዓቶችን እያመረተ ማቅረብ መጀመሩ የሚታወስ ሲሆን፣ የአሁኑ ፋብሪካ መጠናቀቅ ደግሞ ሀገሪቱ በኤሮስፔስ ቴክኖሎጂ ያላትን ተወዳዳሪነት የሚያጎለብት ነው። ይህ ስኬት ኢትዮጵያ ከአውሮፕላን ተጠቃሚነት ባለፈ ወደ አምራችነትና ላኪነት የተሸጋገረችበትን አዲስ ምዕራፍ የሚያበስር ታሪካዊ እርምጃ ሆኖ ተመዝግቧል።
@seledadotio
@seledadotio
- Advertisement -









No comments yet.