ዩኒቨርሲቲዎች ከ30 ዓመት በኋላ ይጠፋሉ – ጠ/ሚ አቢይ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ከሰሞኑ በሁለት ተከታታይ ክፍል በሰጧቸው ቃለ ምልልሶች አነጋጋሪ፣ አወዛጋቢ እና አስደንጋጭ አስተያየቶችን ሰንዝረዋል፡፡
ጠቅላዩ ትምህርትን እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን በተመለከተ የሰጧቸው አስተያየቶች ልብ ሊባሉ የሚገባቸው ናቸው፡፡
በተለይም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ዩኒቨርሲቲዎች ይጠፋሉ ማለታቸው መነጋገሪያ ሆኗል፡፡
‹‹ዩኒቨርሲቲ ምንም ጥርጥር የለውም የዛሬ 30 እና 40 ዓመት ሟቾች ናቸው፤ የ30 እና 40 ዓመት ዩኒቨርስቲ የሚሰለፍ ሰው አይገኝም፤ ዩኒቨርሲቲ 4 እና 5 ዓመት የምትማረውን ትምህርት በ6 ወር በ3 ወር ከቤት መማር ትችላለህ፤ ምንም ጥርጥር የለውም፤ ትሬንዱ ነው እሱን የሚያሳየው። ያም ሆኖ ውስን በጣም ከፍተኛ ጥራት ያላቸው ዩኒቨርስቲዎች ያስፈልጋሉ›› በማለት ሀሰባቸውን አብራርተዋል፡፡
ቀጥለውም፣ ‹‹አሁን ዩኒቨርሲቲዎች ላይ ምርመራ ቢደረግ 1 ሺህ፣ 2 ሺህ ተማሪ መቀበል የሚችል ባዶ ኮንዶሚኒየም ይገኛል። ደሞ የተሰራበት ርካሽ ስለሆነ አይቀጥልም ፈራሽ ነው። እራሱ ዩኒቨርስቲ የእሳቤ ችግር አለበት›› ብለዋል፡፡
‹‹ዩኒቨርስቲ የገነባነው በቂ መዋለህጻናት ያለበት ሀገር ሆኖ ቢሆን ኖሮ ችግር አልነበረውም። በመንግስት የተገነባ 10 መዋለህጻናት አልነበረም ኢትዮጵያ ውስጥ። አንደኛው ዩኒቨርሲቲ ቢተው ኖሮ በኢትዮጵያ ደረጃ ከበቂ በላይ መዋለህጻናት መገንባት ይቻላል ምክንያቱም ቢሊዮኖች ነው የሚወጣባቸው ዩኒቨርሲቲዎች። እኛ ባለፉት 6-7 ዓመታት ከ34 ሺህ በላይ ገንበተናል። ለምን ዋናው ትምህርት የሚያስፈልገው Early Childhood Education ስለሆነ።
@seledadotio
@seledadotio
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ከሰሞኑ በሁለት ተከታታይ ክፍል በሰጧቸው ቃለ ምልልሶች አነጋጋሪ፣ አወዛጋቢ እና አስደንጋጭ አስተያየቶችን ሰንዝረዋል፡፡
ጠቅላዩ ትምህርትን እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን በተመለከተ የሰጧቸው አስተያየቶች ልብ ሊባሉ የሚገባቸው ናቸው፡፡
በተለይም ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ዩኒቨርሲቲዎች ይጠፋሉ ማለታቸው መነጋገሪያ ሆኗል፡፡
‹‹ዩኒቨርሲቲ ምንም ጥርጥር የለውም የዛሬ 30 እና 40 ዓመት ሟቾች ናቸው፤ የ30 እና 40 ዓመት ዩኒቨርስቲ የሚሰለፍ ሰው አይገኝም፤ ዩኒቨርሲቲ 4 እና 5 ዓመት የምትማረውን ትምህርት በ6 ወር በ3 ወር ከቤት መማር ትችላለህ፤ ምንም ጥርጥር የለውም፤ ትሬንዱ ነው እሱን የሚያሳየው። ያም ሆኖ ውስን በጣም ከፍተኛ ጥራት ያላቸው ዩኒቨርስቲዎች ያስፈልጋሉ›› በማለት ሀሰባቸውን አብራርተዋል፡፡
ቀጥለውም፣ ‹‹አሁን ዩኒቨርሲቲዎች ላይ ምርመራ ቢደረግ 1 ሺህ፣ 2 ሺህ ተማሪ መቀበል የሚችል ባዶ ኮንዶሚኒየም ይገኛል። ደሞ የተሰራበት ርካሽ ስለሆነ አይቀጥልም ፈራሽ ነው። እራሱ ዩኒቨርስቲ የእሳቤ ችግር አለበት›› ብለዋል፡፡
‹‹ዩኒቨርስቲ የገነባነው በቂ መዋለህጻናት ያለበት ሀገር ሆኖ ቢሆን ኖሮ ችግር አልነበረውም። በመንግስት የተገነባ 10 መዋለህጻናት አልነበረም ኢትዮጵያ ውስጥ። አንደኛው ዩኒቨርሲቲ ቢተው ኖሮ በኢትዮጵያ ደረጃ ከበቂ በላይ መዋለህጻናት መገንባት ይቻላል ምክንያቱም ቢሊዮኖች ነው የሚወጣባቸው ዩኒቨርሲቲዎች። እኛ ባለፉት 6-7 ዓመታት ከ34 ሺህ በላይ ገንበተናል። ለምን ዋናው ትምህርት የሚያስፈልገው Early Childhood Education ስለሆነ።
@seledadotio
@seledadotio








No comments yet.